Addis Times

Addis Times its new late update and many more

በደቡብ ትግራይ የሚንቀሳቀሰው አርሚ 24 የህወሓት ታጣቂ ተቃዉሞ ማሰማት ጀምሯል!📍ሁኔታው ታጣቂውን ለሚመራው ኮ/ል ካህሳይ መኮንን ለተባለ የቡድኑ አመራርም ራስ ምታት ሆኗል!ፅንፈኛው የህወሓ...
02/02/2026

በደቡብ ትግራይ የሚንቀሳቀሰው አርሚ 24 የህወሓት ታጣቂ ተቃዉሞ ማሰማት ጀምሯል!
📍ሁኔታው ታጣቂውን ለሚመራው ኮ/ል ካህሳይ መኮንን ለተባለ የቡድኑ አመራርም ራስ ምታት ሆኗል!

ፅንፈኛው የህወሓት ቡድን ደቡብ ግንባር በማለት የሚጠራው ታጣቂ የቡድኑን ትዕዛዝ መቀበል እያቆመ እንደመጣ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ እንግዲህ ሃራ መሬት ካለው ሃይል አብዛኛው ከዚህኛው አደረጃጀት የሄደ እንደሆነም ይታወቃል፡፡ ቀሪው ታጣቂም ሰሞኑን ህወሓት በለኮሰው ጦርነት አልሳተፍም በማለት ከቡድኑ አፈንግጦ እየወጣ የሚገኝ ሲሆን በዋናነትም ከአርሚ 44 በርካታ ታጣቂዎች ከነትጥቃቸው ከቡድኑ አፈንግጠው ወጥተዋል፡፡ እንዳይወጡ ቡድኑ ያደረገውን እንቅስቃሴ ተከትሎ ከአርሚ 44 የወጡት ቡድኑ በሰንዓለ ድባቅ እንደመቱት በአይናችን ተመልክተናል፡፡

አሁንም ቢሶበር በሚባል አካባቢ የሰፈረው አርሚ 24 ታጣቂ የሚሰጠውን ትዕዛዝ መቀበል እንዳቆመ የሚደርሱን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ታጣቂ ሃይሉ ወደፊት ውጊያውን እንዲገፋ ከአርሚ አዛዦች የሚወርድለትን አቅጣጫ ከመቀበል ይልቅ ወደኋላ እያፈገፈገ እንደሆነም ከሚደርሱን መረጃዎች ለማወቅ ተችሏል፡፡ ሁኔታው እንዲስተካከል የአርሚ አዛዡ ኮ/ል ካህሳይ መኮንን ከስሩ ለሚገኙት የቡድኑ አመራሮች ትዕዛዝ እያወረደ ቢሆንም የሚሰማውን አጥቷል፡፡

እንዲሁም አጋምሸት የነበረው ሁለት የቡድኑ ሬጅመንት ወደሃራ መሬት መግባቱን የደረሰን መረጃ አመላክቷል፡፡ ከዚህም ውጭ በአርሚ 43 ውስጥም ተመሳሳይ ተቃዉሞ በታጣቂው ዘንድ እየተስተዋለ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል፡፡

የህወሓት እና የሻዕቢያ ጥምረት የትም አይደርስም!ህወሓት ሆነ ሻዕቢያ በእንደ በፊቱ እንዳሻቸው መፈራገጥ አይችሉም። የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት እና አየር ኃይል አሁናዊ ቁመና አለም የመሰከረ...
02/02/2026

የህወሓት እና የሻዕቢያ ጥምረት የትም አይደርስም!

ህወሓት ሆነ ሻዕቢያ በእንደ በፊቱ እንዳሻቸው መፈራገጥ አይችሉም። የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት እና አየር ኃይል አሁናዊ ቁመና አለም የመሰከረለት ግዙፍ ኃይል ሆኗል። ኢትዮጵያ በምድርም ሆነ በሰማይ የማትደፈር ሀገር ሆናለች።

ህወሓት ሆነ ሻዕቢያ የተንኮታኮተ ቡድን ነው። ህወሓት የቀድሞ አቋሙ ተሸርሽሯል። የጌታቸው ረዳ ቡድን፣ ሀራ መሬት የገባው ሀይል፣ ህዝብ ፣ አብዛኛው የቀድሞ ደጋፊው ዲያስፖራው እና አክቲቪስቱ ህወሓትን አይቀበልም። በመንግስት በኩልም አዳብ ካልያዘ መጠፍጠፉ አይቀሬ ነው። ህወሓት ከመፈራገጥ ውጪ ምንም ማምጣት አይችልም። እንደ2013ቱ ካሰበ ተሳስቷል። 1960ዎቹ በሻዕቢያ እና ግብፅ ድጋፍ 4 ኪሎ ገባለሁ ካለ ያዘመነ አልፏል። የህልም እንጀራ ካልሆነ በቀር።🤣

እንዲሁም በሻዕቢያ መንግስት ሲገፉ የኖሩ የቀይ ባህር አፋሮች እና እራሱን ከሻዕቢያ መንግስት የገነጠለው "የኤርትራ ሰማያዊ ፓርቲ" ሻዕቢያን የሚቃውሙ ኃይል ናቸው። የኤርትራ ህዝብ ከ3000 አይበልጥም። ሻዕቢያን የሚቃውም የኤርትራ ህዝብ ቁጥር ደግሞ ቀላል አይደለም። ሻዕቢያ ከኢትዮጵያ ጋር መሳፈጥ አትችልም። ህወሓትን ተትራሶ ኢትዮጵያ ለመውረር ቢያስብም ኤርትራ በተቃዋሚዎች መወረሯ አይቀሬ ነው። ኢሳያስ ትኩረቱን ኢትዮጵያ ላይ ባደረገ ቁጥር ከቤተመንግስት መጠለዙ የማይቀር ይሆናል። ፅምዶ መጥፍያው ነው የሚሆነው።

አሁን ላይ "ፅምዶ" የሚልው የሁለቱ ጥምረት የትም የማይደርስ ነው። ሁለቱም በውስጣቸው ፈረካክሰዋል። ህወሓት ቢፈራገጥ እንጂ ቁቡልነት የለውም። ከመከላከያ ጋር ከገጠመ ደግም ዶግ አመድ መሆኑ አይቀሬ ነው። ፅንፈኛው ፋኖ አግዞኝ የአማራ ክልል የጦር ሜዳን አድርጋለሁ ካለ ፋኖ ስንኩል ከሆነ ሰነባብቷል።

ህወሓት ሆነ ሻዕቢያ ከፉከራ ውጪ ረጅም እርቀት መሄድ አይችሉም። ስለሆነም ባትደክሙ ይሻላል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ሆነ አየር ኃይል በአለም ደረጃ ግዙፍ ኃይል ሆኗል። ሻዕቢያ ሆነ ህወሓት የኢትዮጵያን መከላከያ ሰራዊት በድሮ የምታውቁት አይደለም። በመሆኑም አደብ ግዙ። የምትጋጩት ከግንብ ጋር ነው። በኋላ ጄኖሳይድ እያሉ ማለቃቀስ አይበጅም።

ሰበር መረጃበወልቃይት ጠገዴ ህዝብ በፋኖ ሃይል ከጀርባው ተኩስ ተከፈተበት!እራሱን አፋብን ብሎ የሚጠራው በዘመነ ልካሴ የሚመራው የፋኖ ሃይል በወልቃይት ጥገዴ ህዝብ ላይ ከጀርባው ተኩስ ከፈተ...
02/02/2026

ሰበር መረጃ
በወልቃይት ጠገዴ ህዝብ በፋኖ ሃይል ከጀርባው ተኩስ ተከፈተበት!

እራሱን አፋብን ብሎ የሚጠራው በዘመነ ልካሴ የሚመራው የፋኖ ሃይል በወልቃይት ጥገዴ ህዝብ ላይ ከጀርባው ተኩስ ከፈተበት።የወልቃይት ጥገዴ ህዝብ እራሱን ከጽንፈኛው ህወሃት እየተከላከለ ባለበት ወቅት ጽንፈኛው የፋኖ ቡድን ከሱዳን ድንበር ወደወልቃይት ጥገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ጠገዴ ወረዳ እምባጋላይ ቀበሌ በመግባት በህዝቡ ላይ ተኩስ መክፈቱ ተገለጸ።

በዚህም ተኩስ ህዝቡ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ለማጣል ቢያቅድም በጀግናው የሃገር መከላከያ ሰራዊት እርምጃ የተወሰደበት ሲሆን በከፊል ሲደመሰስ ቀሪዎቹ ደግሞ ተማርከዋል። ከተማረኩት ሃሎች ውስጥ ወደ 17 የሚጠጉ የሻዕቢሃ ወታደሮች እንደሆኑም የተነገረ ሲሆን ይሄም ፋኖ ከሻዕቢያጋር እየሰራ እንዳለ በግጽ አረጋግጧል።

"እምቢ ለዳግም ጦርነት" የሁመራ ህዝብህወሓት ትግራይን ዳግም የጦርነት ቀጠና ለማድርግ በጠለምት ጦርነት የከፈተ ሲሆን ጦርነት ያንገሸገሸው የትግራይ ህዝብ እምቢ ለዳግም ጦርነት በማለት በሁመ...
02/02/2026

"እምቢ ለዳግም ጦርነት" የሁመራ ህዝብ

ህወሓት ትግራይን ዳግም የጦርነት ቀጠና ለማድርግ በጠለምት ጦርነት የከፈተ ሲሆን ጦርነት ያንገሸገሸው የትግራይ ህዝብ እምቢ ለዳግም ጦርነት በማለት በሁመራ እና አካባቢው ህወሓትን የሚያወግዝ ሰላማዊ ሰልፍ እያደረገ ይገኛል። ህወሓት እድሜውን ለማርዘም የትግራይን ህዝብ መጠቀሚያ በማድረግ እንዳሻው ጦርነት የሚያውጅ ሲሆን እንደ ህዝብ የትግራይ ህዝብ ሰላም ወዳድ ህዝብ ነው። ለዚህም በጦርነት መካከል ሆኖ ከሞትንም እንሙት በማለት በሁመራ እና አካባቢው ህዝብ ከማለዳ ጀምሮ አደባባይ በመውጣት "እምቢ ለዳግም ጦርነት እያለ ይገኛል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነገ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ማብራሪያ ይሰጣሉየኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት ...
02/02/2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነገ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ማብራሪያ ይሰጣሉ

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የስራ ዘመኑ10ኛ መደበኛ ስብሰባውን ነገ ያካሂዳል።

ምክር ቤቱ በነገ ስብሰባው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች የሚሰጡትን ምላሽና ማብራሪያ የሚያዳምጥ ይሆናል።

የህወሓት ታጣቂ አመራር የሆነው ኮ/ል ልጃለም በታጣቂው ሽንፈት ምክንያት እራሱን በመሳት ሆስፒታል መግባቱ ታውቋል!!በፀለምት ወረዳ ህወሓት የገጠመውን አስከፊ ሽንፈት ተከትሎ  ተጣቂውን የሚመ...
02/02/2026

የህወሓት ታጣቂ አመራር የሆነው ኮ/ል ልጃለም በታጣቂው ሽንፈት ምክንያት እራሱን በመሳት ሆስፒታል መግባቱ ታውቋል!!

በፀለምት ወረዳ ህወሓት የገጠመውን አስከፊ ሽንፈት ተከትሎ ተጣቂውን የሚመራው ኮ/ል ልጃለም የተባለው የህወሓት ታጣቂ አመራር በድንጋጤ የተነሳ እራሱን ስቶ ከስምሪት ቀጠና በመውጣት በቆላ ተንቤን ወረዳ አቢይአዲ ከተማ እየታከመ እንደሚገኝ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ይህን ተከትሎም ታጣቂው አሁን ላይ ከተሰማራበት አካባቢ እረኛ እንደሌለው ከብት በየ ቦታው እየተበታተነ እና ከአካባቢው ጦርነቱን በመሸሽ ጥሎ እየጠፋ ነው። ይህም የሚያሳዬው በህወሓት ቤት ከፍተኛ የሆነ ሽብር መፈጠሩን ነው። እንደ አጠቃለይ ህወሓት አሁን ላይ የገባበት የጦርነት አዙሪት ከአመራሩ እስከ ታጣቂው ክፉኛ እያመሰው መሆኑን ነው።

No More War!  A ground-shaking rally is underway in Humera today. Residents are vocally opposing TPLF’s provocations, st...
02/02/2026

No More War!
A ground-shaking rally is underway in Humera today. Residents are vocally opposing TPLF’s provocations, stating that the people of Wolkait-Tegede-Setit Humera have no space for outdated agendas. It’s time for stability and growth.

02/02/2026
02/02/2026

የትግራይ ወጣት ነቅሎ ወጣ
ለ80 እና ለ90 አመት አዛውንቶች ተብሎ የ20 አመት ልጅ አይሞትም"

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Times posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share