Yirgalem Construction

Yirgalem Construction Yirgalem Construction is a Grade–1 General Construction Company which
is established as a sole proprietor in 1989 E.C. Operating for over 30 years.

engaged in Buildings, Roads, Water, electro mechanical, treatment plants, and other infrastructure works.

በይርጋለም ኮንስትራክሽን ተቋራጭነት የፌዴራል መንግስት ህንጻዎች ግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤት የሚያሰራው የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ህንጻ ግንባታ በከፍተኛ አመራሮች ተጎበኘ።  የፌዴራል ጠቅላይ...
28/07/2026

በይርጋለም ኮንስትራክሽን ተቋራጭነት የፌዴራል መንግስት ህንጻዎች ግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤት የሚያሰራው የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ህንጻ ግንባታ በከፍተኛ አመራሮች ተጎበኘ።

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ ተዎድሮስ ምህረት እና የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒና ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት አራት ኪሎ ባሻወልዴ ችሎት አካባቢ በመገንባት ላይ የሚገኘውንና ከፊል ርክክብ የተደረገለትን የህንጻ ግንባታ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡

በ #ይርጋለምኮንስትራክሽን ኃ.የተ.የግል ማህበር እየተገነባ የሚገኘው ባለ ሦስት ብሎክ የህንጻ ግንባታ ከፊል ርክክብ ተደርጎለት ስራ የጀመረ ሲሆን የቀሪዎቹን የሁለት ብሎኮች የግንባታ ስራ ለማጠናቀቅ በተሰራው ስራ ከ66 በመቶ በላይ ማድረስ ተችሏል፡፡ ስራው በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑ በከፍተኛ አመራሩ ዕውቅና የተሰጠው ቢሆንም ከተያዘው ጊዜ አንጻር የቀረው ጊዜ አጭር በመሆኑ አሁን ካለው በተሻለ ፍጥነት መጓዝ እንደሚገባ በአመራሮች መመሪያ ተሰጥቷል፡፡

በአማካሪ መሀንዲሱና በህንጻ ተቋራጩ በኩል ስራውን በተባለው ጊዜ አጠናቆ ለማስረከብ በንዑስ ስራ ተቋራጮች አማካኝነት ስራውን ለማሰራት ጥረት እየተደረገ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን ስራውን በተሻለ ፍጥነትና በጥራት ለማከናወን የሰው ኃይሉን ቁጥር ማሳደግና ማጠናከር እንዲሁም የፈረቃ ስራን ተጠቅሞ በተጨማሪ ሰዓት ስራውን በማሰራት ከወትሮው በተለየ አካሄድ መጓዝ እንደሚያስፈልግ ተገልጾላቸዋል፡፡

በመጨረሻም በአመራሮች በተሰጠ ቀጣይ አቅጣጫ ስራው ያለበትን ወቅታዊ ሁኔታ ግምት ውስጥ ያስገባ የማካካሻ ዕቅድ ተዘጋጅቶ የደረሰበት ደረጃ በየጊዜው በቅንጅት እንዲገመገምና ስራው አሁን በተያዘው ግለት በፍጥነትና በጥራት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡

Yirgalem Construction
በጋራ ኢትዮጵያን እንገነባለን!

እንኳን ለአመታዊው  የሀዋሳ ቅዱስ ገብርኤል የንግስ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። Yirgalem Construction
26/07/2026

እንኳን ለአመታዊው የሀዋሳ ቅዱስ ገብርኤል የንግስ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

Yirgalem Construction

የሀዋሳ ከተማ ኮሪደር 4ኛ ዙር በመፋጠን ላይ ነው! ይርጋለም ኮንስትራክሽን የኢትዮጵያን ከተሞን በኮሪደር ልማትና መንገድ ስራ እያሞሸረ ይገኛል። በሀዋሳ ከተማ እየተሰራ ያለው የኮሪደር ልማት...
22/07/2026

የሀዋሳ ከተማ ኮሪደር 4ኛ ዙር በመፋጠን ላይ ነው!

ይርጋለም ኮንስትራክሽን የኢትዮጵያን ከተሞን በኮሪደር ልማትና መንገድ ስራ እያሞሸረ ይገኛል።

በሀዋሳ ከተማ እየተሰራ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ አስፓልት፣ የእግረኛ መንገድ፣ የብስክሌት መንገድ እና የፍሻሽ ቦይ ያካተተ ነው።

በቅርቡ ተጀምሮ ሌት ተቀን በመስራት በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ መጠቀቅ ተቃርቧል። የሀዋሳን ከተማ ውበት ይበልጥ የሚያጎላና የንግድ ትስስርና ቅልጥፍናን በመጨመር ለኑሮ ምቹ የሚያደርግ ነው።

የክልሉን መንግስት፣ የዞኑን እና የከተማ አስተዳደር ለምታደርጉልን ድጋፍ እና ክትትል ምስጋናችን ላቅ ያለ ነው።

በጋራ ኢትዮጵያን እንገነባለን።

ይርጋለም ኮንስትራክሽን - ሀዋሳ

ይርጋለም ኮንስትራክሽን በጥራት ጎዳና ድርጅታችን ይርጋለም ኮንስትራክሽን በጥራት ሽልማት ድርጅት ባለሙያዎች የሚካሄደውን የ13ኛ ዙር የጥራት ዉድድር ግምገማ ከአርብ ጀምሮ በዋና መስሪያ ቤታች...
29/06/2026

ይርጋለም ኮንስትራክሽን በጥራት ጎዳና

ድርጅታችን ይርጋለም ኮንስትራክሽን በጥራት ሽልማት ድርጅት ባለሙያዎች የሚካሄደውን የ13ኛ ዙር የጥራት ዉድድር ግምገማ ከአርብ ጀምሮ በዋና መስሪያ ቤታችን - ሀዋሳ ፣ ሰኔ 19፣ 2018 ዓ.ም. (June 26, 2026) አካሂዷል።

ግምገማው አጠቃላይ የድርጅቱን አሰራር፣ በጥራት ላይ ያለውን ቁርጠኝነት፣ በተያያዘም የሰራተኛ፣ የፕሮጀክት፣ የፋይናንስ እንዲሁም የማቴሪያል ማኔጅመንት ላይ ያተኮረ ነበር።

በግምገማው ወቅትም የጥራት ሽልማት ድርጅት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ቴድሮስ መብራት፣ የድርጅታችን መስራችና ባለቤት ኢንጂነር ዘላለም ወ/አማኑኤልና የማኔጅመንት አባላት ተሳታፊ ነበሩ።

በዚህ አስፈላጊ የግምገማ ሂደት ጥራት ሽልማት ድርጅት ላደረጉልን ሙያዊ ድጋፍና መመሪያ ከልብ እናመሰግናለን።

We are pleased to announce that our organization Yirgalem Construction has commenced the 13th Round competition Evaluation by experts from the Ethiopian Quality Award Organization (EQA) . The assessment began on Friday at our head office, June 26, 2026, Hawassa. It contains all the necessary evalution of the Projects, Finance, Human Resource and Leadership Management practices.

We thank all the assessors on the valuable guidance and professional support provided throughout this important evaluation process.

የረዳንን እግዚአብሄርን እናመሰግናለን!

For all new and updates follow us on
Website: https://yirgalemconstruction.com
Facebook: https://facebook.com/yirgacons
Tiktok: https://www.tiktok.com/
Instagram: https://instagram.com/yirgacon
Telegram: https://t.me/yirgacon
Twitter: https://x.com/yirgacon
Youtube: https://www.youtube.com/
Linkedin: https://www.linkedin.com/company/yirgacon
Tiktok: https://www.tiktok.com/

በጋራ ኢትዮጵያን እንገነባለን!

ይርጋለም ኮንስትራክሽን!

‎ይርጋለም ኮንስትራክሽን በሲዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በይርጋዓለም የተ/የግብ/ኢን/ ፓርክ ተጨማሪ ሦስት አዳዲስ ፕሮጀክቶች ትግበራ ላይ የውል ስምምነት ተፈራረመ። ‎የኢንጂነር...
17/06/2026

‎ይርጋለም ኮንስትራክሽን በሲዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በይርጋዓለም የተ/የግብ/ኢን/ ፓርክ ተጨማሪ ሦስት አዳዲስ ፕሮጀክቶች ትግበራ ላይ የውል ስምምነት ተፈራረመ።

የኢንጂነር ዘላለም ወልደአማኑኤል ዱባለ ድርጅቶች ውስጥ የሆኑት የሦስት ፕሮጀክቶች ትግበራ ስምምነት በዛሬው ዕለት ተፈርሟል፡፡

‎ቀደም ሲል በ”Golden organic Avocado oil’’ ምርት ላይ ተሰማርተው ያሉት ኢንጂነር ዘላለም ወልደአማኑኤል በዛሬው ዕለት ስምምነቱን የፈረሙት በፓርኩ ተጨማሪ ሶስት ፕሮጀክቶች ማለትም በዘርፈብዙ የጥራጥሬ ዘይት፣ የድፍድፍ ዘይት ማጣሪያ እና የተቀናጀ የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ፕሮጀክቶች ናቸው፡፡

‎ፕሮጀክቶቹ በ12.8 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ወይንም 2 ቢሊዮን ብር የሚፈጁ ፕሮጀክቶች ሲሆኑ፤ በሙሉ አቅም ወደ ሲራ ሲገባ ለ500 ያህል ወጣቶች ቋሚ የስራ ዕድል የሚፈጥሩ ይሆናል፡፡

‎የውል ስምምነቱን የፈረሙት ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ ኃይሉ የተራ እንደገለጹት በፓርኩ የሀገር ውስጥ ባለሀብት በዚህ ያህል ካፒታል ፕሮጀክት ሲፈረም የመጀመሪያ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት ረገድ እጅግ ትልቅ ፋይዳ ያላቸው ፕሮጀክቶች መሆናቸውንም አመላክተዋል፡፡

‎የፕሮጀክቱ ባለቤት የሆኑት ኢንጂነር ዘላለም ወልደአማኑኤል በበኩላቸው ፕሮጀክቶቹ ቀደም ሲል በነበረው የአቮካዶ ዘይት ፕሮጀክት ተበረታተው የጀመሯቸው መሆኑን ገልፀው፤ የሶስቱንም ፕሮጀክቶች ሼድ ግንባታ በአጭር ጊዜ ውስጥ አጠናቀው ወደ ምርት ሂደት እንደሚገቡ አረጋግጠዋል፡፡

የድርጅታችን ሰራተኞችና ማናኔጅምነት አካላት እንኳን ደስ አለን፣ አላችሁ!

የረዳን ፈጣሪ ይመስገን!

በጋራ ኢትዮጵያን እንገነባለን!

ይርጋለም ኮንስትራክሽን

ጎልደን አቮካዶ ዘይት ማምረቻ ፋብሪካ ግብአት መጠኑን አሳደገ። የይርጋለም ኮንስትራክሽን እህት ኩባንያ የሆነው ጎልደን አቮካዶ ዘይት ማምረቻ ፋብሪካ ከማህበራት ከሚረከበው አቮካዶ በተጨማሪ በ...
10/06/2026

ጎልደን አቮካዶ ዘይት ማምረቻ ፋብሪካ ግብአት መጠኑን አሳደገ።

የይርጋለም ኮንስትራክሽን እህት ኩባንያ የሆነው ጎልደን አቮካዶ ዘይት ማምረቻ ፋብሪካ ከማህበራት ከሚረከበው አቮካዶ በተጨማሪ በሎካ አባያ የራሱ እርሻ/Farm/ ትልቅ ምርት ሰብስቧል።

ፋብሪካው በይርጋለም አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ የሚገኝ ሲሆን በውስጡ በርካታ ፋብሪካዎችን ይዟል።

በአመት እስከ 80,000 ገበሬዎችን ካቀፉ ህ/ስራ ማህበራት የሚረከብ ይህም በተጨማሪ ለውጭ ሀገር የሚላከውን ምርት ከፍ ያደርገዋል።

ፋብሪካው በእርሻና እንዱስትሪ ላይ በመሰማራት ለሀገራችን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ እያመጣ መሆኑ ይታወቃል።

ይርጋለም ኮንስትራክሽን
ጎልደን አቮካዶ ፋብሪካ

🌹ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛዉ ዓመተ ሂጅራ የታላቁ ኢድአል አድሃ አረፋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር እና የአንድነት ይሁንላችሁ ✨🌙Eid Mub...
27/05/2026

🌹ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛዉ ዓመተ ሂጅራ የታላቁ ኢድአል አድሃ አረፋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር እና የአንድነት ይሁንላችሁ ✨🌙

Eid Mubarak ✨ 🌙
Yirgalem Construction

24/05/2026

የጅግጅጋ ተለዋጭ መንገድ ግንባታን አስመልክቶ
እንኳን ደስ አላችሁ!
©ኢቢሲ

Yirgalem Construction

22/05/2026

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yirgalem Construction posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Yirgalem Construction:

Shortcuts

Share