29/03/2024
የጨረታ ማስታወቂያ
ለእግረኛ መንገድ ታይልስ አምራች ድርጅቶች በሙሉ፤
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በተለያዩ የከተማዋ ክፍሎች ለሚገነባቸው የእግረኛ መንገዶች ንጣፍ የሚውል ደረጃውን የጠበቀ ታይልስ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም በጨረታው የሚሳተፉ የታይልስ አምራቾች፡-
1ኛ/ የሚያመርቱትን ታይልስ ዲዛይን እና የጥራት ደረጃ ማረጋገጫ፣
2ኛ/ የሚያቀርቡትን ታይልስ የካሬ ሜትር እና የነጠላ ዋጋ፣
3ኛ/ በቀን የማምረት አቅምን የሚያሳይ የተረጋገጠ ማስረጃ፣
4ኛ/ የታደሰ የንግድ ፈቃድ እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን ሰርተፍኬት)፣
5ኛ/ በማህበር የተደራጁ ከሆነ በሚመለከተው አካል የተደራጁበትን እና ወደ ስራ እንዲገቡ የተሰጠ ማረጋገጫ
ሰነዶችን በማያያዝ ይህ ማስታወቂያ ከተነገረበት ቀን ጀምሮ እስከ መጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ አዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን ዋና መስሪያ ቤት ቢሮ ቁጥር 107 በስም በታሸገ ኢንቨሎፕ በማቅረብ እንዲወዳደሩ ይጋብዛል፡፡
አድራሻ፡- ሳር ቤት ከአዳምስ ፓቪሊዮን ህንጻ ጎን
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን