12/04/2026
የፓኪስታን መርከቦች ተመለሱ‼️
ሁለት የፓኪስታን ባንዲራ የያዙ ባዶ የነዳጅ ታንከሮች ከኩዬት እና የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ነዳጅ ለመጫን በሆርሙዝ የባህር ሰርጥ ለማለፍ ተቃርበው የነበረ ቢሆንም መመለሳቸውን ፋርስ ኒውስ ዘግቧል።
እነዚህ ነዳጅ የጫኑ መርከቦች የተመለሱት በኢራን ትዕዛዝ ሳይሆን ትራምፕ የአሜሪካ የባህር ኃይል በሆርሙዝ ሰርጥ ለማለፍ የሚሞክሩትን ማንኛውንም እና ሁሉንም መርከቦችን የማገድ ሂደት መጀመሩን መናገራቸውን ተከትሎ መሆኑን ዘገባው ጠቅሷል። ፓኪስታን ድርድሩ ባይሳካም የአሜሪካ እና የኢራንን ድርድር አመቻች ሀገር እንደነበረች ይታወቃል።
Truth