20/09/2025
የአበሽጌ ወረዳ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፅ/ቤት በኢትዮ ኮደር ስልጠና የተሻለ ውጤት በማስመዝገቡ የእውቅና ሠርተፍኬት ተበረከተለት።
መስከረም 10/2018 ዓ.ም (ወልቂጤ)
የጉራጌ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ የ2017 በጀት አመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2018 በጀት እቅድ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በወልቂጤ ከተማ የምክክር መድረክ በዛሬው እለት አካሂደዋል።
በዚህም የአበሽጌ ወረዳ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፅ/ቤት ፣ የ2017 በጀት አመት እቅድ አፈጻጸም የተሻለ በማስመዝመዝገብ ማጠናቀቅ መቻሉ ተገልጿል።
በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ በንቅናቄ እንዲመራ የተደረገዉ የ5 ሚሊየን ኮደሮች ኢንሼቲቭ የተሻለ በማስመዝገብ ፣ስርቲፋይ በማድረግ ከዞኑ ካሉ መዋቅሮች 100% እና ከዛም በላይ በማምጣት የእውቅና ሰርተፊኬት ተሸላሚ ሆኖአል።