Lij Elias University-The Amharic College of Science

Lij Elias University-The Amharic College of Science science
Technology
Engineering online store only

ግንቦት 26 ቀን 1992 ዓ.ምከ 26 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን የፊደል ገበታ አባት አርበኛው ቀኛዝማች ተስፋ ገብረሥላሴ ያረፉበት ዕለት ነበር።  ‹‹ሀ ሁ…እውቀት ይስፋ…ድንቁርና ይጥፋ…...
06/03/2026

ግንቦት 26 ቀን 1992 ዓ.ም
ከ 26 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን የፊደል ገበታ አባት አርበኛው ቀኛዝማች ተስፋ ገብረሥላሴ ያረፉበት ዕለት ነበር።
‹‹ሀ ሁ…እውቀት ይስፋ…ድንቁርና ይጥፋ…ይህ ነው የኢትዮጵያ ተስፋ…›› ተስፋ ገብረ-ሥላሴ ዘብሔረ ቡልጋ.....
ኢትዮጵያ የራሷ የሆነ ፊደል ያላት አገር ናት፡፡ ይህም ከበርካታ የዓለም አገራት ተለይታ እንድትታይ ከሚያደርጓት መገለጫዎቿ መካከል አንዱ ነው፡፡ ይህ የኢትዮጵያ ፊደል በመላ አገሪቱ ተስፋፍቶ አገራዊ መገለጫነቱ ይዳብርና ብዙዎችም ማንበብና መፃፍ ችለው ከመሃይምነት ያመልጡ ዘንድ የአንድ ኢትዮጵያዊ ጠቢብ ርዕይና ጥረት ያስፈልግ ነበር፡፡ ይህ አርቆ አሳቢ ጠቢብ ቀኛዝማች ተስፋ ገብረሥላሴ ይባላሉ፡፡
ታህሣሥ 24 ቀን 1895 ዓ.ም ሰሜን ሸዋ ፣ ቡልጋ ውስጥ አክርሚት በተባለ ስፍራ በመምህር ገብረሥላሴ ቢልልኝ እና ወ/ሮ ሥዕለአብ ወ/ሚካኤል ቤት ይችን ዓለም የተቀላቀለው ልጅ ‹‹ተስፋ›› የሚል ስም ተሰጠው፡፡ 4 ዓመት ሲሞላውም ከአባቱ እግር ስር ተቀምጦ ፊደል መቁጠር ጀመረ፡፡
የሕፃኑ ተስፋ ወላጆች አራሽ ገበሬዎችና ከብት አርቢዎች ስለነበሩ፣ ተስፋ እያደገ ሲሄድ ከትምህርቱ ይልቅ ወደ ከብት ጥበቃው እንዲያተኩር ተደረገ፡፡ ተስፋ ከትምህርት ይልቅ ከብት ጥበቃ ላይ እንዲያተኩር መደረጉ ያልተዋጠላቸው የተስፋ አያት መሪጌታ ቢልልኝ ተስፋን እንዲያስተምሩላቸው መምህር ገ/አብ ለተባሉ የቤተክህነት ሊቅ ወስደው ሰጧቸው፡፡
መምህር ገብረአብም ሕፃኑን በደስታ ተቀብለው ንባብን ፣ ዳዊትን ፣ ውዳሴ ማርያምን ፣ መልክዓ ማርያምን ፣ መልክዓ ኢየሱስንና ሰዓታት ዘሌሊትን አስተምረው በድቁና አስመረቁት፡፡ ተስፋ ድቁናውን ከተቀበለ በኋላም በአክርሚት ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ማገልገል ጀመረ፡፡
የተስፋ አባት መምህር ገብረሥላሴ ከቅስና ሙያቸውና ከግብርና ስራቸው በተጨማሪ በትርፍ ጊዜያቸው ከእፅዋት ቀለም እያነጠሩ ለፀሎትና ለአብያተ ክርስቲያናት አገልግሎት የሚሰጡ መጻሕፍትን በብራና ይፅፉና ያዘጋጁ ነበር፡፡ በጊዜው ግብር የሚከፈለው አዲስ አበባ ነበር፡፡ ግብር መክፈያ ወቅቱ ሲደርስና ነጋዴዎቹ እንደ ሚመጡ ሲያውቅ ፣ ነጋዴዎቹን ከኋላ ከኋላ እየተከተለ ፣ እነርሱ ሳያዩት ወደ አዲስ አበባ ተጓዘ፡፡
ነጋዴዎቹ ብዙ ርቀት ከተጓዙ በኋላ ተስፋን አዩት፡፡ ወደኋላ እንዳይመልሱት ብቻውን ሊሆን ነው፡፡ ስለሆነም ይዘውት አዲስ አበባ ገቡ፡፡ ለ 5 ቀናት ያህል ከነጋዴዎቹ ጋር በእግሩ ተጉዞ አዲስ አበባ ደረሰ፡፡ በወቅቱ ቤተመንግስት ውስጥ ሥራ ወደነበራቸው ወደ ታላቅ ወንድሙ ብርሃኔ ገ/ሥላሴ ዘንድ ቀረበ፡፡
ታላቅ ወንድሙ ሲያዩት ፣ ‹‹እንዴት መጣህ? ለመሆኑስ እናትና አባታችን ሰምተዋል?›› ብለው በጥያቄ ሲያፋጥጡት ተስፋ ‹‹አልተናገርኩም›› ይላል። ‹‹በል አሁን ገብተህ እረፍና አብረውህ ከመጡት ሰዎች ጋር ትመለሳለህ›› ብለው አስገቡት።
ከጥቂት ቀናት በኋላ ወደ ትውልድ ስፍራው ሲመለስ ልቡም ዓይኑም ወደ ኋላ ዕየተመለከተ ፣ ‹‹እዚህማ ተመልሼ እመጣለሁ ፤ እስኪ የሚከለክለኝን አያለሁ›› እያለ እየዛተ ነበር፡፡ እንዳሰበውም አልቀረም በ 1909 ዓ.ም ተመልሶ ወደ አዲስ አበባ ሄደ፡፡
ታላቅ ወንድሙም ‹‹በል እንግዲህ ልብህ አላረፈም፤ መልሼም አልሰድህም፡፡ አንድ ክፍል ቤት አለችኝ ፤ እዚያች እረፍና የምትፈልገውን ትሰራለህ›› አሉት፡፡ ከተማውን ከተለማመደ በኋላም ተስፋ ራሱን ለመቻል ሲል ሱቅ በደረቴ ሆኖ ስራ ጀመረ፡፡ መርፌ ቁልፍ፣ ምላጭ ፣ መፋቂያና የመሳሰሉትን እያዞረ ይሸጥ ነበር፡፡ ከዚያም ታላቅ ወንድሙን ብድር ጠየቀ፡፡ የ75 ሳንቲም ብድር፡፡
በዚያች 75 ሳንቲም በወቅቱ ታዋቂ የነበረ ሽቶ ይሸጥ ነበር፡፡ ይህ ሽቶ ከፈረንሳይ በጅቡቲ በኩል አድርጎ ነበር የሚመጣው። ሽቶውን ወደ ኢትዮጵያ የሚያስመጡ ነጋዴዎችም ነበሩ። ተስፋ ሽቶውን በ 75 ሳንቲም ገዝቶ ‹‹እሪ በከንቱ›› ወደሚባለው ሰፈር በመሄድ በሰፈሩ ላሉ ሴቶች በትርፍ ይሸጣል፡፡ ከዚህ ሽያጭ በሚያገኘው ገንዘብ መጽሐፍ ገዝቶ ይሸጥ ነበር፡፡ አዲስ አበባ በገባ በዓመቱ ፣ በወርሃ በየካቲት 1910 ዓ.ም ዘመን ተሻጋሪ የኢትዮጵያውያን ባለውለታ የሚያደርገውን ተግባር አከናወነ፡፡
የፊደል ገበታን አዘጋጀ፡፡ የተስፋ አባት መምህር ገብረሥላሴ ከእፅዋት ቀለም እያነጠሩ ለፀሎት እና ለአብያተ ክርስቲያናት አገልግሎት የሚሰጡ መጻሕፍትን በብራና ይፅፉና ያዘጋጁ ስለ ነበር ተስፋም የአባቱን ፈለግ ተከትሎ የፍየል ቆዳ በእንጨት ላይ በመወጠር እየፋቀ ፣ ቀለሙን ከልዩ ልዩ እፅዋት እያነጠረና ፊደላትን በመቃ ብዕር እየፃፈ በማራባት ወገኑን የሚጠቅም ስራ ያከናውን ጀመር፡፡
በዚያ ጊዜ ግዕዝም ሆነ አማርኛ ማንበብና መፃፍ ፣ በቤተ ክህነትና በቤተመንግስት የተገደበ እንጂ ሰፊው ህዝብ ዘንድ አልተዳረሰም ነበር፡፡ ስለዚህ ለሰዎች መፅሐፍ ቅዱስ በግዕዝም በአማርኛም ካነበበላቸው በኋላ ፣ ‹‹በሉ ግዙ፤ ይጠቅማችኋል›› ሲላቸው ፣ ‹‹አንተን አብረን ካልገዛን ማን ያነብልናል? ልጆቻችን አያውቁም ፤ እኛም አናነብም›› ይሉት ነበር፡፡ በዚህ ጊዜ ነው ‹‹እንዲህ ሰርቼ ፣ እንዲህ ቢማሩ ፣ በኋላ የተለያዩ መፅሀፎችን እያዘጋጀሁ እሸጣለሁ ፤ እኔም እጠቀማለሁ…›› ብሎ ሩቅ በማሰብ መጻሕፍትን ማዘጋጀት የጀመረው፡፡
በ 1921 ዓ.ም ማተሚያ ቤት በማቋቋም ‹‹እውቀት ይስፋ ፤ ድንቁር እና ይጥፋ ፤ ይህ ነው የኢትዮጵያ ተስፋ›› የሚለውን ኃይለ ቃል አርዕስት በመስጠት ፊደልን ፣ ፊደለ ሐዋርያንና አቡጊዳን በሦስት ረድፎች እያዘጋጀ በማሳተም በመላ ኢትዮጵያ ማሰራጨት ጀመረ፡፡ በርካታ ኢትዮጵያውያን በተለይም በገጠራማ አካባቢዎች የሚኖሩ ሰዎች ከፊደላት ጋር ተዋወቁ፡፡
የእውቀት ብርሃንን በመላ አገሪቱ የማዳረስ ዓላማ በፋሺስት ኢጣሊያ ወረራ ምክንያት ሊሰናከል በተቃረበበት ጊዜ ተስፋ ራሱ ባዘጋጀው የፊደል ገበታ ተጠቅሞ አርበኝነቱን ጀመረ፡፡ ፋሺስት ኢጣሊያ ኢትዮጵያን የመውረሯ ጉዳይ እርግጠኛ እየሆነ በመጣበት ወቅት እንዲህ በማለት ጽፎ ለሕዝቡ አሰራጨ፡፡
‹‹ከባሕር እየወጣ መጣልን አሳው ፣
በሰይፍ እየመተርን ባረር እቆላን ፈጥነን እንብላው ፣
ጥንት አባቶቻችን ምግባቸው ይህ ነው ፣
ምነው ያሁን ልጆች ዝምታው ምንድን ነው ፣
የባሕሩ አሳ ወጥቶ ከጎሬው ፣
አጥማጁ አንቆ እንጂ ስጋውን ይብላው፡፡››
ተስፋ ይህን መሰል ወኔ ቀስቃሽ ጽሑፎችን እያዘጋጁ በማተምና በማባዛት በመላ ኢትዮጵያ በማሰራጨት ሕዝቡ አገሩን ከወራሪው ኃይል ለመከላከል እንዲነሳ አድርገዋል፡፡ ፋሺስት ኢጣሊያ ኢትዮጵያን መውረር በጀመረችበት ወቅት አንዳንድ የኢትዮጵያን ባለስልጣናትን በገንዘብ እየደለለች የስለላና የማስከዳት ስራ ስትጀምር ተስፋ የዳግማዊ አፄ ምኒልክን ፎቶ የጽሑፉ አርማ በማድረግ የዓድዋ ጀግኖች የፈፀሙትን አኩሪ ተግባር መድገም እንጂ ለገንዘብና ለስልጣን ብሎ አገርን ለጠላት አሳልፎ መስጠት እጅግ አሳፋሪ ተግባር መሆኑን ለመግለፅ:
‹‹የተረገመ ነው አገሩን የከዳ ፣
ክብሩን ነፃነቱን ሀበሻን የጎዳ፡፡
ከኢትዮጵያ (ከሀበሻ) ጠላት ጉቦ የበላችሁ ፣
የት ነው የምትበሉት አገር ሳይኖራችሁ፡፡
ያልታመኑ ሌቦች ከሹመት ተሸረው ፣
አገሪቱን ይምሩ ታማኞች ተመርጠው›› በማለት ስለሁኔታው ሃሳባቸውን በግጥም አቅርበው ነበር፡፡
ተስፋ እነዚህንና መሰል ጽሑፎችን እያተመ በብዛት ሲያሰራጭ አገር በመክዳት የተጠረጠሩት ባለስልጣናት ብቻ ሳይሆኑ ወረራውን የሚቃወሙትና የከዳተኞቹን ድርጊት የሚያወግዙት ሹማምንት ጭምር ያጉረመርሙ ጀመር፡፡ በጊዜው ይታተሙ የነበሩ ጽሑፎች ሁሉ በጽሕፈት ሚኒስቴር ሳይመረመሩና ፈቃድ ሳይሰጣቸው ማሰራጨት የተከለከለ ስለነበር ተስፋ ተይዞ እንዲቀርብና በየክፍላተ አገሩ አሳትሞ ያሰራጫቸው ጽሑፎችም እንዲሰበሰቡ ታዘዘ፡፡
ተስፋም ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ፊት ቀርቦ ‹‹በመላ ኢትዮጵያ ያሰራጨኸውን ስብከት የት ነው ያሳተምከው?›› ተብሎ ተጠየቀ፡፡ እርሱም ‹‹በሊቀ ጳጳሱ አቡነ ቄርሎስ ግቢ ውስጥ ባለው ማተሚያ ቤት ነው›› ብሎ መለሰ፡፡ በዚህም ምክንያት ሊቀ ጳጳሱ ‹‹ስለምን በብፁዕነትዎ ግቢ ውስጥ ወንጀል ተሰራ?›› ተብለው ሲጠየቁ ‹‹አገራችሁን አትካዱ ፤ ከጠላት ጉቦ አትቀበሉ› ብሎ መስበኩ ወንጀልነቱ ምንድን ነው?…›› ብለው መልስ ሰጡ፡፡ ጉዳዩ እንዲጣራ ተወስኖ ተስፋ በማረፊያ ቤት እንዲቆይ ተደረገ፡፡ ወዲያውኑም የፋሺስት ኢጣሊያ ወረራ እየገፋ በመምጣቱ ያለመንግሥት ፈቃድ እንዲህ ዓይነት ጽሑፎችን እንዳያትምና እንዳያሰራጭ ዋስ ጠርቶ ከእስር ተፈታ፡፡
ጦርነቱ በተፋፋመበት ወቅትም ተስፋ ሕዝቡ ለነፃነቱ እንዲታገል የሚቀሰቅሱ ጽሑፎችን እያሳተሙ ከማሰራጨት አልቦዘነም ነበር፡፡ ለአብነት ያህል የኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ ባለው መሳሪያ ጠላትን እንዲከላከልና እጁን አጣጥፎ እንዳይቀመጥ የሚያሳስብና ‹‹የኢትዮጵያ ፋና›› የሚል ርዕስ ያለው ጽሑፍ እያሳተመ ያሰራጭ ነበር፡፡
የፋሺስት ኢጣሊያ ጦር አዲስ አበባን ሲቆጣጠር ተስፋ ታሰረ፡፡ በመኖሪያ ቤቱ የነበሩትን ጽሑፎች ቀደም ብሎ በመደበቁ በፋሺስቶች ዘንድ እንደወንጀለኛ የሚያስቆጥረው ነገር ስላልተገኘበት ከእስር ተፈታ፡፡ ከእስር ከተፈታ በኋላም ጽሑፎችን በማተምና በማሰራጨት አርበኞችን የማነቃቃት ስራውን ቀጠለበት፡፡
ፋሺስት ኢጣሊያ ኢትዮጵያን በወረረችበት ወቅት (1928 ዓ.ም - 1933 ዓ.ም) ብዙዎች በዱር በገደል ሆነው ወራሪውን ኃይል ፋታ ነስተው ታላቅ የአርበኝነት ተጋድሎ ባደረጉበት ወቅት ፣ ተስፋ ገብረሥላሴ የተለያዩ ወረቀቶችን እያባዛ የአገር ፍቅር ስሜትን የሚኮረኩር ፤ የአርበኞችን ጀግንነትም የሚገልጹ ጽሑፎችን በከተማ ይበትን ነበር፡፡
ተስፋ በመልዕክቶቹ አርበኛው እንዳይበተንና ኅብረቱን አጠንክሮ እንዲፋለም ከማሳሰብ ባሻገር የአርበኞች ማኅበር እንዲቋቋም ሃሳብ ካቀረቡ ሰዎች መካከል አንዱ ነበር፡፡ በዚህ ምክረ ሃሳብ መሰረትም የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር በ 1931 ዓ.ም ሊቋቋም ችሏል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የፋሺስት ኢጣሊያ አገዛዝ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ይፈፅም የነበረውን ግፍና በደል በወቅቱ ለንደን ይገኙ ለነበሩት ንጉሠ ነገሥት ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ደብዳቤ በመላክ ያሳውቁ ነበር፡፡
ከዚህ በኋላ ተስፋ በድጋሜ በፋሺስት ወታደሮች ታሰረ፡፡ ማተሚያ ቤቱም ተወረሰበት፡፡ በእስር ቤቱ ውስጥም እስረኞች በረሀብና በውሃ ጥም መጎዳታቸውን ተመለከተ፡፡ የእስር ቤቱን ኃላፊ አስጠርቶ ‹‹… አርባ ማር ትሬዛ ብር ስላለኝ ይፈቀድልኝና ዳቦ ገዝቼ ላብላቸው…›› ብሎ ጠየቀ፡፡ የእስር ቤቱ ኃላፊም በተስፋ አነጋገር ስሜቱ በመነካቱ ብዙ ዳቦ ፣ ሻይና ውሃ መጥቶ ለእስረኞች እንዲታደላቸው በማድረጉ እስረኛውን ሁሉ በረሀብና በውሃ ጥም ከማለቅ ታደገው፡፡
ከወራሪው የፋሺስት ኢጣሊያ ኃይል መባረር በኋላ ተስፋ ሰላማዊ ኑሮ ለመምራት ጥረት ማድረግ ጀመሩ፡፡ ማተሚያ ቤቱንም በአዲስ መልኩ በማጠናከር ‹‹ሀ ሁ… እውቀት ይስፋ …ድንቁርና ይጥፋ… ይህ ነው የኢትዮጵያ ተስፋ.. ›› ብለው ጽሑፎችን ማሳተም እና ማሰራጨት ቀጠሉ፡፡ በዚህ ስራቸውም ትምህርትን በመላ ኢትዮጵያ ለማዳረስና መሃይምነትን ለማጥፋት ከፍተኛ አስተዋፅዖ አበርክተዋል፡፡ ዘመናዊ የሕትመት መሳሪያዎችን ከውጭ በማስመጣት ስራቸውን አስፋፉ፡፡
‹‹ሀ ሁ››ን ፣ ‹‹አቡጊዳ››ንና ‹‹መልዕክተ ዮሐንስ››ን ጨምሮ በአጠቃላይ ከ 300 በላይ መፅሐፍትን ማዘጋጀትና ማሳተም ችለዋል፡፡ የፊደል ገበታን ቀርፀው መሃይምነትን ለማጥፋት ካበረከቱት አስተዋፅኦ በተጨማሪ በአርበኝነት ትግላቸው ላደረጉት ተጋድሎ የቀኝ አዝማችነት ማዕረግ ተሰጥቷቸዋል፡፡
ቀኛዝማች ተስፋ ገብረሥላሴ ለስራ እጅግ የተለየ ክብር ነበራቸው፡፡ 97ኛ ዓመት የልደት በዓላቸውን ሲያከብሩ‹‹ … ሆዴ እህል በልቶ ቢጠግብም እጄን ስራ ይርበዋል …›› በማለት ለስራ ያላቸውን ጉጉትና አክብሮት ገልፀው ነበር፡፡ እድሜያቸው ገፍቶ እንኳ በድርጅታቸው ዋና መስሪያ ቤት እየተገኙ የስራውን ሂደት ይቆጣጠሩና እርሳቸውም ኃላፊነታቸውን ይወጡ ነበር፡፡
ቀኛዝማች ተስፋ ገብረሥላሴ ከእፅዋት የቀለም ዱቄት ቀምመውና በጥብጠው ፣ ከመቃ እንጨት ብዕር ቀርጸው በወረቀት ላይ ፊደል በመፃፍ በካርቶን ላይ እየለጠፉ በማቅረብ ሚሊዮኖችን ከመሃይምነት ያወጡና የእውቀትን ብርሃን የፈነጠቁ ታላቅ የአገር ባለውለታ ናቸው፡፡
‹‹ያነበበ እውቀትን ጠገበ ፣
ድንቁርናን ክዶ ወደ እውቀት ተሳበ ፣
የጥበብን ገጿን ለማየት ቀረበ›› የሚለው ግጥም ቀኛዝማች ተስፋ ገብረሥላሴን የሚመለከት ይመስላል፡፡
ቀኛዝማች ተስፋ የስራቸውን አስፈላጊነትና የትምህርትን ጥቅም ሲያስረዱ ‹‹ማንኛውም ሰው እናት አገሩ ባስገኘችለት፤ ሊቃውንት አባቶች አዘጋጅተው ባቆዩለት ፊደል ተምሮ ማንበብና መፃፍ ተቀዳሚ ተግባሩ ይሆናል፡፡ መምህራንም የፊደላትን ስነ ባሕርይ ማስረዳት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ይህም በየጊዜው የሚነሳው ብሔራዊ ትውልድ ራሱን ክዶ ሌላውን ሆኖ እንዳይገኝ ወይም ‹መነሻውን አያውቅ መድረሻውን ይናፍቅ› ከመሰኘት ነፃ ያደርገዋል›› ብለው ነበር፡፡
ቀኛዝማች ተስፋ ገብረሥላሴ በስራቸው ላይ ከጎናቸው ሆነው ሲያበረታቷቸውና ሲደግፏቸው ከኖሩት ወይዘሮ አለሚቱ ንጉሤ ጋር ጋብቻ መስርተው 13 ልጆችን አፍርተዋል፡፡ በሕይወት እስከ ነበሩበት ጊዜ ድረስ 42 የልጅ ልጆችንም ዐይተዋል፡፡
‹‹ሀ ሁ … እውቀት ይስፋ… ድንቁርና ይጥፋ … ይህ ነው የኢትዮጵያ ተስፋ...›› ብለው በማወጅ ድንቁርናን ለማፋት በመላ ኢትዮጵያ የፊደል ሰራዊትን ሲያዘምቱ የኖሩት አርበኛው ቀኛዝማች ተስፋ ገብረሥላሴ ግንቦት 26 ቀን 1992 ዓ.ም አርፈው ስርዓተ ቀብራቸው በማግሥቱ ግንቦት 27 ቀን 1992 ዓ.ም በቅዱስ ራጉኤል ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡

“እውቀት ይስፋ ፣ ድንቁርና ይጥፋ
ይህ ነው ለኢትዮጵያ ብሩህ ተስፋ።"

የዛሬ 63 ዓመት የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በ32 አገሮች አባልነት ሲመሰረት የድርጅቱ ቻርተር (የቃል-ኪዳን ሰነድ) በአማርኛም ጭምር ተዘጋጅቶ መሪዎቹ የፈረሙበት መሆኑን ስንቶቻችን እናውቅ ...
05/27/2026

የዛሬ 63 ዓመት የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በ32 አገሮች አባልነት ሲመሰረት የድርጅቱ ቻርተር (የቃል-ኪዳን ሰነድ) በአማርኛም ጭምር ተዘጋጅቶ መሪዎቹ የፈረሙበት መሆኑን ስንቶቻችን እናውቅ ይሆን?

05/25/2026

የአማርኛ ኮሌጅ ሳይንስ (አኮሳ) ምናባዊ ክፍል አጠቃቀም

ዶ/ር አበራ ሞላ የግዕዝ ፊደላት በኮምፒዩተሮች ላይ እንዲጻፉ እና እንዲታተሙ የሚያስችል ዘዴ በማዘጋጀት በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና አግኝተዋል - ይህ ስኬት በኢትዮጵያ ቋንቋዎች ዲጂታል ግን...
05/23/2026

ዶ/ር አበራ ሞላ የግዕዝ ፊደላት በኮምፒዩተሮች ላይ እንዲጻፉ እና እንዲታተሙ የሚያስችል ዘዴ በማዘጋጀት በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና አግኝተዋል - ይህ ስኬት በኢትዮጵያ ቋንቋዎች ዲጂታል ግንኙነት አብዮትን የፈጠረ ነው። በዚህም ከፍተኛ አስተዋጽኦ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ አማካኝነት የኢትዮጵያን የቋንቋ ቅርስ በመጠበቅና በማስተዋወቅ ረገድ ታሪካዊ እድገትን አሳይተዋል።

የልጅ ኤልያስ ዩኒቨርሲቲ በአማርኛ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የሳይንስና የምህንድስና ትምህርት ለማቅረብ ተልዕኮውን ሲቀጥል፣ የዶ/ር አበራ ሞላ እውቀት የአካዳሚክና የቴክኖሎጂ መሠረታችንን ለማጠናከር ወሳኝ ሚና ይጫወታሉ።

ዶ/ር አበራ ሞላ ከልጅ ኤልያስ ዩኒቨርሲቲ ጋር ወደፊት በሚያደረጉት የትብብር የጋራ ሥራ ራዕይን እንጋራለን፤ ይህም የወደፊት ትውልዶችን የኢትዮጵያ ምሁራን በራሳቸው ቋንቋ እንዲማሩ፣ እንዲፈጥሩ እና እንዲመሩ ማብቃት ነው። የኢትዮጵያን እውቀትና ባህል ለማሳደግ ያደረጉት ቁርጠኝነት በብሔራዊ ማንነት እና በሳይንሳዊ ልቀት ላይ የተመሠረተ ለውጥ የሚያመጣ የትምህርት ንቅናቄ የመገንባት የጋራ ግባችን ፍጹም የሚስማማ ነው።

Dr. Abera Molla has earned international recognition for developing a method for writing and printing Ge’ez characters on computers – an achievement that has revolutionized the digital communication of Ethiopian languages. His significant contributions have also marked a historic step forward in preserving and promoting Ethiopian linguistic heritage through modern technology.

As Lj Elias University continues its mission to provide world-class science and engineering education in Amharic, Dr. Abera Molla’s expertise will play a vital role in strengthening our academic and technological foundations.

Dr. Abera Molla shares a common vision for his future collaboration with Lj Elias University; which is to empower future generations of Ethiopian scholars to learn, create, and lead in their own language. His commitment to advancing Ethiopian knowledge and culture is perfectly aligned with our goal of building a transformative education movement based on national identity and scientific excellence.

🎓 ታሪካዊ ክንዋኔ፡- የመጀመሪያውን የኢንጂነሪንግ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ ማስጀመርዛሬ፣ ግንቦት 11፣ 2026፣ ከአራት ሳምንታት በኋላ በኢትዮጵያ ውስጥ ከቆየሁ በኋላ በዴንቨር የቴክኖሎጂ ማዕ...
05/11/2026

🎓 ታሪካዊ ክንዋኔ፡- የመጀመሪያውን የኢንጂነሪንግ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ ማስጀመር
ዛሬ፣ ግንቦት 11፣ 2026፣ ከአራት ሳምንታት በኋላ በኢትዮጵያ ውስጥ ከቆየሁ በኋላ በዴንቨር የቴክኖሎጂ ማዕከል ወደሚገኘው ዋና ቢሮአችን ተመልሻለሁ - ይህም ጥልቅ፣ አነቃቂ የግንባታ እና የማቀናጀት ጊዜ ነው። በዚህ ጉብኝት ወቅት፣ ጠንካራ የፋኩልቲ ቡድን አደራጅተን በአማርኛ እንደ የትምህርት ቋንቋ የሚቀርቡ የምህንድስና ፕሮግራሞችን ለመጀመሪያ ጊዜ የመስመር ላይ ምዝገባ ለመጀመር ተዘጋጅተናል። ይህ ምዕራፍ በኢንጂነሪንግ ትምህርት ተደራሽነት፣ ፍትሃዊነት እና የላቀ እድገትን የሚያጎላ ኩራት የሚንጸባረቅበት እርምጃ ነው።
🌍የምህንድስና ትምህርት አዲስ ዘመን
ይህ ዩኒቨርሲቲ በአምስት የምህንድስና ፕሮግራሞች የመጀመሪያ ዲግሪዎችን ይሰጣል፤ እነሱም የኬሚካል ምህንድስና ፣ የኤሌክትሪክ ምህንድስና፣ የሜካኒካል ምህንድስና፣ የማዕድን ምህንድስና እና የፋውንድሪ ቴክኖሎጂ ናቸው። እያንዳንዱ ፕሮግራም በአማርኛ ቋንቋ እንደ ዋና የትምህርት ቋንቋ በመስመር ላይ የሚቀርብ ሲሆን ይህም ለረጅም ጊዜ በቋንቋ እና በጂኦግራፊ እንቅፋቶች ዝቅተኛ አገልግሎት ላገኙ ተማሪዎች እድልን ያሰፋዋል። ምዝገባው ለመማር ለሚፈልጉ ከማንኛውም ሀገር ተማሪዎች ክፍት ነው፣ ይህም በልጅ ኤልያስ ዩኒቨርሲቲ የሚመራ የአካዳሚክ ሞዴልን በእውነት ዓለም አቀፍ ተደራሽነትን ያመጣል። ከሁሉም በላይ ደግሞ ይህ የዚህ አይነት የምህንድስና ዲግሪ ፕሮግራሞች በመስመር ላይ የሚገኙበት የመጀመሪያው ጊዜ ሲሆን ይህም በመማሪያ ልምዱ መሃል ላይ የአማርኛን ቋንቋን ለሳይንስ ትምህርት ግብዓት ይጠቀማል።
📚 የፕሮግራም አወቃቀር እና የጊዜ መስመር
የላብራቶሪ ኮርሶች ቁልፍ ዝመና፡- በአሁኑ የትምህርት ፖሊሲዎች ምክንያት፣ የላብራቶሪ ኮርሶች መጀመሪያ እንደታቀደው ወዲያውኑ ሳይሆን በሁለተኛው ዓመት ይጀምራሉ። ይህ ማስተካከያ በመጀመሪያው ዓመት ውስጥ ካለው የመጀመሪያ ራዕይ ጋር ሙሉ በሙሉ የተገደበ ነው፣ ነገር ግን የተሟላውን የፕሮግራም ተሞክሮ እየገነባን ስንቀጥል ተገዢነትን ያረጋግጣል።

✨ ያሳካነው ነገር
በአራት ሳምንታት የኢትዮጵያ ጉብኝት ወቅት ጠንካራና ብቁ የሆነ የመምህራን ቡድን አሰባስቧል
ለኦንላይን የምዝገባ ስርዓት የተቋቋመ መሠረተ ልማት
ለአምስቱ የምህንድስና ፕሮግራሞች በአማርኛ ትምህርት የተዘጋጀ ሥርዓተ ትምህርት አዘጋጅቷል
ለአለም አቀፍ ተማሪዎች የመግቢያ መንገዶችን ፈጥሯል
ፕሮግራሙን ለማስጀመር የትምህርት ፖሊሲ መስፈርቶችን ተሻሽሏል

ወደፊት ስመለከት፣ ይህ ምዕራፍ በተለያዩ ሀገራት ለሚገኙ ተማሪዎች በቀላሉ ተደራሽ በሆነ መንገድ ምህንድስናን ለመከታተል ዝግጁ ለሆኑ ተማሪዎች ስለሚኖረው ተጽእኖ ተስፋ አደርጋለሁ። በአማርኛ ከፍተኛ ጥራት ያለው የምህንድስና ትምህርት ማቋቋም የማካተት ጉዳይ ብቻ አይደለም - ለፈጠራ፣ ለሠራተኛ ኃይል እድገት እና ለረጅም ጊዜ ለአገር አቀፍ እና ለክልላዊ ልማት አነቃቂ ነው። በራዕዩ ላይ ሙሉ በሙሉ ቁርጠኝነት አለን፣ እናም ይህንን ታሪካዊ ጅምር ወደ ዘላቂ ለውጥ ስንቀይር ፕሮግራሙን በየዓመቱ ማጠናከራችንን እንቀጥላለን።

🎓 Historic Milestone: Launching Ethiopia's First Online Engineering University
Today, May 11, 2026, I’m back at our head office in Denver Tech Center after four weeks in Ethiopia—an intensive, inspiring period of building and alignment. During this visit, we organized a strong faculty team and prepared to launch the first-ever online enrollment for engineering programs delivered with Amharic as the language of instruction. This milestone marks a proud step forward for access, equity, and excellence in engineering education.
🌍 A New Era in Engineering Education
This university will offer first degrees in five engineering programs: Chemical Engineering, Electrical Engineering, Mechanical Engineering, Mining Engineering, and Foundry Technology. Each program is delivered online with Amharic as the primary language of instruction, expanding opportunity for learners who have long been underserved by language and geography barriers. Enrollment is open to students from any nation who want to learn, bringing a truly global reach to Lij Elias University-The Amharic College of Science academic model. Most importantly, this is the first time engineering degree programs of this kind are available online with Amharic instruction at the center of the learning experience.
📚 Program Structure & Timeline
Key update on lab courses: Due to current education policies, lab courses will begin in the second year rather than immediately as originally planned. This adjustment has limited full engagement with the initial vision in the first year, but it ensures compliance while we continue building toward the complete program experience.

✨ What We've Accomplished
Assembled a strong, qualified faculty team during the 4-week Ethiopia visit
Established infrastructure for an online enrollment system
Developed curriculum for five engineering programs with Amharic instruction
Created pathways for international student enrollment
Navigated education policy requirements to launch the program

Looking ahead, I’m optimistic about the impact this milestone will have for students across nations who are ready to pursue engineering through a more accessible pathway. Establishing high-quality engineering education in Amharic is not only a matter of inclusion—it is a catalyst for innovation, workforce growth, and long-term national and regional development. We remain fully committed to the vision, and we will continue strengthening the program year by year as we turn this historic launch into lasting transformation.

04/26/2026
ዛሬ በታላቅ ትህትና በቅዱስ አባታችን ፊት ቀርቤ ለብርሃነ ትንሳኤ የእንኳን አደረሶት መልካም ምኞቴን ለመግለጽ በመታደሌ ታላቅ ክብርና ደስታ ተሰምቶኛል። በሀገሬ ምድር ተገኝቼ ይህንን የመሰለ...
04/23/2026

ዛሬ በታላቅ ትህትና በቅዱስ አባታችን ፊት ቀርቤ ለብርሃነ ትንሳኤ የእንኳን አደረሶት መልካም ምኞቴን ለመግለጽ በመታደሌ ታላቅ ክብርና ደስታ ተሰምቶኛል። በሀገሬ ምድር ተገኝቼ ይህንን የመሰለ መንፈሳዊ ዕድል ማግኘቴ ልዩ ቀን ሆኖልኛል።

ዶ/ር  ባለሟል  አጥናፉወደ ልጅ ኤልያስ ዩኒቨርሲቲ እንኳን በደህና መጡ!የልጅ ኤልያስ ዩኒቨርሲቲ ዶ/ር ባለሟል አጥናፉን ለተከበሩት የመምህራን ፋከልቲ በኩራት ተቀብሏቸዋል። ዶ/ር ባለሟል ዩ...
04/15/2026

ዶ/ር ባለሟል አጥናፉ
ወደ ልጅ ኤልያስ ዩኒቨርሲቲ እንኳን በደህና መጡ!

የልጅ ኤልያስ ዩኒቨርሲቲ ዶ/ር ባለሟል አጥናፉን ለተከበሩት የመምህራን ፋከልቲ በኩራት ተቀብሏቸዋል። ዶ/ር ባለሟል ዩኒቨርሲቲውን የሚቀላቀሉት በጆኦሎጂና የማዕድን ምህንድስና ዘርፍ ከቅድመ መሰረቱ ሲሆን በኢትዮጵያ ውስጥ መሰረት በምንጥልበት ወሳኝ ወቅት፣ ከተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም እስከ ኢንዱስትሪ ምስረታ ለምናፈራቸው የሰለጠነ የሰው ኃይል ዝግጅቶች ተቋሙ ሳይንስና ቴክኖሎጂን በአማርኛ ቋንቋ የማስተማር ተልዕኮውን ለማራመድ እና ለመስራት ከሚሹ የተከበሩ ምሁር ናቸው።

የዶ/ር ባለሟል መምጣት በዩኒቨርሲቲው የትምህርት ጉዞ ውስጥ ጉልህ የሆነ ምዕራፍ ነው። የእሳቸው እውቀት፣ ቁርጠኝነት እና የምሁራዊ ብቃት የልጅ ኤልያስ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ ቋንቋ እና ባህል ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፍ የትምህርት አካባቢ ለመፍጠር ያለውን ራዕይ መሰረት ያጠናክራሉ።

ስለ ዶ/ር ባለሟል አጥናፉ

ዶ/ር ባለሟል አጥናፉ በሳይንሳዊ ምርምርና በከፍተኛ ትምህርት ጠንካራ ልምድ ያላቸው የተከበሩ ምሁርና አስተማሪ ናቸው። የአካዳሚክ አስተዋፅዖዎቻቸውና የአመራር ልምዳቸው ዩኒቨርሲቲው በኢትዮጵያ የሳይንስ ትምህርት ውስጥ በቲዎሪና በተግባር መካከል ያለውን ክፍተት ለማጥበብ ካለው ተልዕኮ ጋር ፍጹም ይጣጣማሉ።

በአማርኛ ቋንቋ እውቀትን ለማሳደግ ያለንን ቁርጠኝነትም ሆነ ትግበራ ለተማሪዎቻችን በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው የሚያስቡ፣ አዳዲስ ፈጠራዎችን የሚያመጡ እና የሚግባቡ አዲስ የሳይንስ ሊቃውንትና መሐንዲሶች ትውልድ እንዲፈጠር አስተዋጽኦ ያደርጋሉ።

ዶ/ር ባለሟል የአካዳሚክ ፕሮግራሞችን በማዘጋጀትና በመምራት፣ የመምህራንን ምክር በመስጠት እና በአማርኛ ላይ የተመሰረቱ የሳይንስና የምህንድስና ሥርዓተ ትምህርቶችን በመፍጠር ረገድ ቁልፍ ሚና ይጫወታሉ። የልጅ ኤልያስ ዩኒቨርሲቲ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ካምፓስ ለመገንባትና የአካዳሚክ ተደራሽነትን ለማስፋት የሚያደርገውን ጉዞ ሲቀጥል የአመራር ሚናቸው ወሳኝ ይሆናል።

ዶ/ር ባለሟል አጥናፉ እንኳን በደህና መጡ። የእርስዎ አስተዋጽኦ በልጅ ኤልያስ ዩኒቨርሲቲ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍን ያጎላል - ይህም ለእውቀት፣ ለፈጠራ እና ለብሔራዊ ኩራት የሚደረግ እንቅስቃሴ ነው።

Welcome to Lij Elias University
Dr. Balemwal Atnafu
Date: April 15, 2026
Location: Addis Ababa, Ethiopia

A Warm Welcome

Lij Elias University proudly welcomes Dr. Balemwal Atnafu to its distinguished faculty. Dr. Balemwal joins the university at a pivotal moment in its growth and transformation, as the institution continues to advance its mission of teaching science and technology in the Amharic language.

Dr. Balemwal’s arrival marks a significant milestone in the university’s academic journey. His expertise, dedication, and scholarly excellence will strengthen the foundation of Lij Elias University’s vision to create a world-class educational environment rooted in Ethiopian language and culture.

About Dr. Balemwal Atnafu

Dr. Balemwal Atnafu is a respected scholar and educator with a strong background in scientific research and higher education. His academic contributions and leadership experience align perfectly with the university’s mission to bridge the gap between theory and practice in Ethiopian science education.
His commitment to advancing knowledge through the Amharic language will inspire both faculty and students, contributing to the creation of a new generation of scientists and engineers who think, innovate, and communicate in their native language.

Message from the Leadership
Looking Ahead

Dr. Balemwal will play a key role in developing and guiding academic programs, mentoring faculty, and contributing to the creation of Amharic-based science and engineering curricula. His leadership will be instrumental as Lij Elias University continues its journey toward building a world-class campus and expanding its academic reach.

Welcome aboard, Dr. Balemwal Atnafu.

Your contribution marks a new chapter in the story of Lij Elias University — a movement for knowledge, innovation, and national pride.

አመት ከአመት ያድርሰን ተቋማችንን የተቋሞች አውራ ያድርግልን፣ ኢትዮጵያን የአፍሪካ አውራ ያድርግልን።ይህ የተስፋፋ ራዕይ፤ ተቋማችን በእያንዳንዱ ዓመት እየተጠናከረ እንዲሄድ፣ በኢትዮጵያና በ...
04/14/2026

አመት ከአመት ያድርሰን ተቋማችንን የተቋሞች አውራ ያድርግልን፣ ኢትዮጵያን የአፍሪካ አውራ ያድርግልን።

ይህ የተስፋፋ ራዕይ፤ ተቋማችን በእያንዳንዱ ዓመት እየተጠናከረ እንዲሄድ፣ በኢትዮጵያና በአፍሪካ ውስጥ የትምህርትና የሳይንስ ብርሃን የምናስፋፋ ያድርገን።

ተቋማችን የእውቀት መሠረት እንዲሆን እና በአማርኛ ቋንቋ የሳይንስን ትምህርት እንዲያበራ ያፅናን።

ኢትዮጵያ በአፍሪካ ውስጥ የትምህርትና የቴክኖሎጂ መሪ እንድትሆን ሳንታክት እንድንሰራ ይርዳን።

የተቋማችንን እያንዳንዱ አመት የትምህርትን እና የሳይንስን ብርሃን በኢትዮጵያ ላይ እንዲጨምር ፈጣሪ አምላክችን ቅዱስ እግዚአብሔር እውቀትና ማስተዋል ያብዛልን።

Address

Greenwood Village, CO

Opening Hours

Monday 9am - 5pm
Tuesday 9am - 5pm
Wednesday 9am - 5pm
Thursday 9am - 5pm
Friday 9am - 5pm

Telephone

+17209854298

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Lij Elias University-The Amharic College of Science posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Lij Elias University-The Amharic College of Science:

Share