28/05/2026
፦ የ12 ዓመቷ ታዳጊ አዜብ በላይነህ የደረሰችበት አልታወቀም
በሲዳማ ክልል ምስራቃዊ ዞን፣ በንሳ ወረዳ ዳዬ ከተማ ባለፉት ቀናት በማኅበራዊ ሚዲያና በአካባቢው ማኅበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ስጋትና ቁጭትን የፈጠረው የታዳጊዋ መታፈን ጉዳይ፣ እስካሁን ድረስ ምንም ዓይነት ፍንጭ ሳይገኝለት 11 ቀናትን አስቆጥሯል።
ገና የ12 ዓመት ዕድሜ ያልሞላትና የአንደኛ ደረጃ ተማሪ የሆነችው ታዳጊ አዜብ በላይነህ በዕለቱ ግንቦት 9 ቀን 2018 ዓ.ም (ከቀኑ 8:00 አካባቢ) ወደ እምነት ተቋም ለመሄድ ከቤቷ ትወጣለች።
ሆኖም ግን ማንነታቸው ባልታወቁ ግለሰቦች አማካኝነት፣ በአንድ ባለሦስት እግር ተሽከርካሪ (ባጃጅ) ውስጥ በኃይል ተገዳና እየጮኸች መታፈኗን የአይን እማኞች ጠቁመዋል።
የአካባቢው ነዋሪዎችና ቤተሰቦቿ ድምፅ ሰምተው ለማስጣል ጥረት ቢያደርጉም፣ ተሽከርካሪው በከፍተኛ ፍጥነት ከአካባቢው በመሰወሩ ሳይሳካ ቀርቷል።
ታዳጊዋ ተጠልፋ ከተወሰደችበት ዕለት ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ሙሉ በሙሉ አድራሻዋ የጠፋ ሲሆን፣ ወላጆቿና የቅርብ ዘመዶቿ በከፍተኛ የሥነ-ልቦና ስቃይና በዕንባ ውስጥ ይገኛሉ።
ቤተሰቦቿ እንደሚገልጹት፣ ጉዳዩን ለሚመለከተው አካል ቢያመለክቱም እስካሁን ድረስ የሚጠበቀውን ያህል ፈጣንና ተገቢውን ክትትል እያገኙ እንዳልሆነ በምሬት ይናገራሉ።
"ሕግ የቆመበት ዓላማ የዜጎችን ደኅንነት ለመጠበቅ ካልሆነ ታዲያ ለምንድነው?" የሚለው ጥያቄ በአሁኑ ወቅት የብዙዎችን ልብ የነካና ምላሽ የሚሻ ሆኗል።
ይህች ተጫውታ ያልጠገበችና የቤተሰቧ ተስፋ የሆነች ጨቅላ ሕፃን ወደ ወላጆቿ እቅፍ በሰላም እንድትመለስ እና ፍትህ እንድታገኝ የሁላችንም ሰብዓዊ ግዴታ ነው።
መረጃው ሰፊ ተደራሽነት አግኝቶ ለሚመለከታቸው ከፍተኛ የጸጥታ አካላትና ለሕዝብ እንዲደርስ ፍትህ ለአዜብ በላይነህ" በማለት ጽሑፉን በስፋት Share እና Comment በማድረግ አጋርነታችሁን እንድታሳዩ በትሕትና እንጠይቃለን።
ማንኛውንም ፍንጭ ወይም መረጃ ካላችሁ በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች በአስቸኳይ እንድታሳውቁ ተማጽነናል፦
* 0916031825
* 0960927729
* 0937210547
የሕፃን ልጅ ዕንባና የቤተሰብ እሮሮ ዝም ሊባል አይገባም፤ መረጃውን ለሌሎች በማጋራት የበኩላችንን እንወጣ!