14/06/2026
የደብረ ማርቆስ አየር ማረፊያ የበረራ አገልግሎት በይፋ ተጀመረ
አዲስ አበባ — የሀገሪቱን የውስጥ በረራ ተደራሽነት ይበልጥ ለማስፋፋት እየሰራ የሚገኘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ወደ ደብረ ማርቆስ ከተማ የሚያደርገውን የቅድመ-ምረቃ በረራ ዛሬ ሰኔ 6 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ መጀመሩን አስታውቋል።
ይህ አዲስ መዳረሻ የአየር መንገዱን የረጅም ጊዜ የአገልግሎት ማሻሻያና የማስፋፊያ ስትራቴጂ አካል መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ ተጓዦችን ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ጋር በቅርበት እንደሚያገናኝ ይጠበቃል።
የበረራ አገልግሎቱ መጀመር በአካባቢው ነዋሪዎች፣ በነጋዴዎችና በአየር መንገዱ ሰራተኞች ዘንድ ከፍተኛ መነቃቃትንና ደስታን ፈጥሯል።
ይፋዊው በረራ መጀመሩ በተለይም ለንግድና ኢንቨስትመንት አዳዲስ የኢኮኖሚና የልማት ዕድሎችን ይዞ እንደሚመጣ የታመነበት ሲሆን፣ የክልሉን የቱሪዝም እንቅስቃሴም በከፍተኛ ደረጃ ያሳድጋል።
የመጀመሪያው ዙር መንገደኞች ለአሚኮ በሰጡት አስተያየት፣ የአየር ትራንስፖርቱ መጀመር ቀደም ሲል በየብስ ይፈጅ የነበረውን ረጅም ሰዓትና ድካም ያስቀረ በመሆኑ ትልቅ የጊዜና የገንዘብ እፎይታ ሰጥቶናል ብለዋል።
አዲሱ የደብረ ማርቆስ በረራ በክልሉ የሚስተዋለውን የትራንስፖርት ፍላጎት በዘመናዊ መልኩ ለመቅረፍ እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ለማጠናከር ትልቅ ሚና እንደሚጫወትም ተመልክቷል።
Via አሚኮ