14/03/2026
!
!
ከሀገራዊ የሰሌዳ ለውጥ ጋር ተያይዞ፣ በትራንስፖርት እና ሎጂስቲክ ሚኒስትር ደረጃ እየተሰራ መሆኑ ይታወቃል። በዚህም ምክንያት አልፎ አልፎ፣ በተለይ የአአ ኮድ 03 እና የኢት ኮድ 03 ሰሌዳ እጥረት ገጥሞን የነበረ መሆኑ ይታወሳል። ነገር ግን የፌዴራል ፐብሊክ ሰርቪስ ትራንስፖርት አገልግሎት የሰሌዳ እጥረቱን በዘላቂነት ለመፍታት እየሰራ ይገኘል። በአሁኑ ሰዓት በሁሉም ቅርንጫፎቻችን ምንም ዓይነት የሰሌዳ እጥረት አለመኖሩን በመገንዘብ፣ ያለ ምንም ውጣ ውረድ እና እንግልት ወደ ተቋማችን እየመጣችሁ መገልገል የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
7766