3A Engineering

3A Engineering This is the official page of 3A Engineering

01/04/2026

!
፡ መንግሥት በነዳጅ አቅርቦት ላይ አዳዲስና ጠንከር ያሉ ውሳኔዎችን አስተላለፈ::

አዲስ አበባ - መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣው ቀውስ እና የዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ መናጋትን ተከትሎ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የአቅርቦት እጥረቱን ለመቋቋም የሚያስችሉ ተከታታይ ውሳኔዎችን ማሳለፉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ዛሬ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል::

ሚኒስትሩ እንደገለጹት፣ ከጦርነቱ በፊት 80 ዶላር የነበረው የአንድ በርሜል ነጭ ናፍጣ ዋጋ በአሁኑ ወቅት ወደ 230 ዶላር አሻቅቧል። በተመሳሳይ ቤንዚን ከ70 ወደ 150 ዶላር ደርሷል።

ኢትዮጵያ ቀደም ሲል የነበራት የነዳጅ ግዥ ውል በአቅራቢ አገራት ምክንያት በመስተጓጎሉ፣ 180 ሺህ ሜትሪክ ቶን ነዳጅ ሳይቀር መቅረቱን ጠቁመዋል።

ይህም የናፍጣ የቀን አቅርቦት ከ9.2 ሚሊዮን ሊትር ወደ 4.5 ሚሊዮን ሊትር እንዲቀንስ አድርጎታል።

የተፈጠረውን እጥረት በፍትሐዊነት ለመምራት መንግሥት ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን የቅድሚያ አሰጣጥ ሥርዓት ዘርግቷል። በዚህም መሠረት ነዳጅ በቅድሚያ የሚያገኙት፦

1. ነዳጅ ጫኝ ተሽከርካሪዎች (ለስርጭት ቅድሚያ ይሰጣቸዋል)

2. ከፍተኛ አምራችና ላኪ ድርጅቶች (በቀጥታ እንዲያገኙ ይደረጋል)

3. መሠረታዊ የፍጆታ ዕቃዎችን የሚያጓጉዙ ተሽከርካሪዎች

4.ግብርናን የሚያዘምኑ ትራክተሮችና ማሽነሪዎች

5. የብዙኃን ትራንስፖርት (አውቶቡሶችና በናፍጣ የሚሰሩ የሕዝብ ማመላለሻዎች)

ሁኔታውን 24/7 የሚከታተል "ልዩ ኦፕሬሽን ክፍል" በማዕከል ደረጃ ተቋቁሟል። እስካሁን በተደረገ ክትትል በሕገ-ወጥ ተግባር የተሳተፉ 658 ግለሰቦች (የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ) በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን፣ 720 ሺህ ሊትር ነዳጅ ተይዞ ለመንግሥት ገቢ ሆኗል።

ምንም እንኳን የዓለም ዋጋ በሦስት እጥፍ ቢጨምርም፣ መንግሥት በነጭ ናፍጣ ላይ በአንድ ሊትር 95 ብር፣ በቤንዚን ላይ ደግሞ 42 ብር ድጎማ እያደረገ ይገኛል። እስካሁን በአጠቃላይ 262 ቢሊዮን ብር ለድጎማ ወጪ ተደርጓል።

ሚኒስትሩ ወቅታዊውን ችግር በጋራ ለመሻገር ዜጎች የሚከተሉትን ተግባራት እንዲያከናውኑ ጥሪ አቅርበዋል፦

1. ነዳጅን በከፍተኛ ቁጠባ መጠቀም።

2. የአጭር ርቀት ጉዞዎችን በእግር የመጓዝ ባህልን ማዳበር።

3. አላስፈላጊ የጉዞ ፕሮግራሞችን መሰረዝ።

4. በነዳጅ ግብይት ላይ የሚታዩ ሕገ-ወጥ ድርጊቶችን ለሚመለከተው አካል ማጋለጥ።

Via ENA

Pic. ጉርሻ page

Address

Addis Ababa
251

Opening Hours

Monday 02:00 - 20:00
Tuesday 02:00 - 20:00
Wednesday 02:00 - 20:00
Thursday 02:00 - 20:00
Friday 02:00 - 20:00
Saturday 02:00 - 20:00
Sunday 02:00 - 20:00

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when 3A Engineering posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share