Areka Agricultural Research Center, SEARI

Areka Agricultural Research Center, SEARI Government organization, National Enset research program coordination centre.

የኢልኒኖ ተጽዕኖ ተቋቁሞ በአጭር ጊዜ ምርት በሚሰጡ ሰብል ዝርያዎች አ/አደሮችንና በማህበር የተደራጁ ስራ-አጥ ወጣቶችን የመደገፍ ስራ እየተሰራ ይገኛል።ነሐሴ 25 ቀን 2018 ዓ.ም #አረካ፤...
01/09/2026

የኢልኒኖ ተጽዕኖ ተቋቁሞ በአጭር ጊዜ ምርት በሚሰጡ ሰብል ዝርያዎች አ/አደሮችንና በማህበር የተደራጁ ስራ-አጥ ወጣቶችን የመደገፍ ስራ እየተሰራ ይገኛል።

ነሐሴ 25 ቀን 2018 ዓ.ም
#አረካ፤
ማዕከሉ የኢልኒኖ ተጽዕኖ ተቋቁሞ በአጭር ጊዜ ምርት በሚሰጡ ሰብል ዝርያዎች አ/አደሮችንና በማህበር የተደራጁ ስራ-አጥ ወጣቶችን የመደገፍ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ የማዕከሉ ዳይሬክተር ገነነ ገዛኸኝ(ዶ/ር) ገልጸዋል።

አየር ንብረት ለውጥ የሚያመጣውን ተፅዕኖ በአርሶ አደር ያስከተለውን ጉዳት ለመካካስ ማዕከሉ የራሱን ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት ድርቅን የሚቋቋሙና የመድረሻ ጊዜያቸው አጭር የሆኑ ሰብል ዝርያዎችን በቦሎሶ ሶሬ፣በአረካ ከተማ፣በዳሞት ጋሌ፣በዳሞት ሶሬ እና በድጉና ፋንጎ ወረዳዎች ከ86 ሄ/ር በላይ መሳ መሸፈኑን የማዕከሉ ቴክኖሎጂ ሽግግርና ኮሙኒኬሽን ምርምር ስ/ሂደት አስተባባሪ የሆኑት አቶ ታደለ ህርጎ ገልጿል።ቦሎቄ SER-125 ፣አረካ-1 ጤፍ ፣ CR-37ጤፍ፣በላም አተር፣በስንዴ ዝሪያዎች ለአ/አደርና በስራ እድል ፈጠራ ላይ የተደራጁ ወጣቶች ድጋፍ ተደርጓል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት አረካ ምርምር ማዕከል የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እና የእውቅና አሰጣጥ መርሃ-ግብር አካሄደ።ነሐሴ 12 ቀን 2018 ዓ.ም  አ...
18/08/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት አረካ ምርምር ማዕከል የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እና የእውቅና አሰጣጥ መርሃ-ግብር አካሄደ።

ነሐሴ 12 ቀን 2018 ዓ.ም
አረካ፣

የደቡብ ኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት አረካ ምርምር ማዕከል የ2018 በጀት ዓመት አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ፣ የዕቅድ አቅጣጫ ማስቀመጫ እንዲሁም የላቀ አፈጻጸም ላሳዩና ለትምህርት ለወጡ ሠራተኞች የእውቅናና የምስጋና መስጠት መርሃ-ግብር በዛሬው ዕለት በደመቀ ሁኔታ አካሂዷል።

የማዕከሉ የበጀት ዓመቱ አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት በማዕከሉ ዳይሬክተር በዶ/ር ገነነ ገዛኸኝ የቀረበ ሲሆን፣ በተከናወኑ የምርምር፣ ቴክኖሎጂ ሽግግር እና መነሻ ቴክኖሎጂ እና ዘር ብዜት ሥራዎች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
እየተከሰተ ላለውና በቀጣይ ሊከሰት የሚችለውን የኤልኒኖ (El Niño) ተፅዕኖ እና ድርቅን የሚቋቋሚ ሰብሎችንና ቴክኖሎጂዎችን በመስኖ ጭምር በስፋት የማለማመድና የማባዛት ሥራ በትኩረት መሠራት እንደሚገባ የማዕከሉ ዳይሬክተር ዶ/ር ገነነ ገዛኸኝ ገልጸው፣ ለተግባራዊነቱም አስፈላጊው ቅድመ-ዝግጅት እንዲደረግ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

የማዕከሉ የሰው ሀብት ልማት አስተዳደር አስተባባሪ ሳ/ን ትዕግስቱ ማዳ እንዳብራሩት፣ ማዕከሉን ቀደም ሲል በሥራ ሂደት አስተባባሪነት ያገለገሉና እና ለትምህርት ለወጡ የቀድሞ ሠራተኞች የምስጋና ምስክር ወረቀት እንዲሁም በበጀት ዓመቱ በየዘርፋቸው የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ሠራተኞች የዕውቅና ምስክር ወረቀት እንደሚበረከትላቸው ገልጸዋል።

በመጨረሻም መርሃ-ግብሩ በበጀት ዓመቱ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ሠራተኞች እና ለትምህርት ለወጡ የቀድሞ የሥራ ሂደት አስተባባሪዎች የዕውቅናና የምስጋና ምስክር ወረቀት በመስጠት ተጠናቋል።
#አረካምርምርማዕከል #ደቡብኢትዮጵያግብርናምርምርኢንስቲትዩት #የግብርናምርምር #ኢትዮጵያ

የ2018 በጀት ዓመት ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ለአጠቃላይ ሠራተኞች እየቀረበ ይገኛል።
18/08/2026

የ2018 በጀት ዓመት ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ለአጠቃላይ ሠራተኞች እየቀረበ ይገኛል።

በማዕከሉ ከ27 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የሚገነባ የከርሰ ምድር ውኃ ቁፋሮ የቦታ ርክብክብ ተደረገ።አረካ: ነሐሴ 8 ቀን 2018 ዓ.ም   ‎‎ኢንስቲትዩቱ  በአረካ ግብርና ምርምር ማዕከል ለአ...
15/08/2026

በማዕከሉ ከ27 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የሚገነባ የከርሰ ምድር ውኃ ቁፋሮ የቦታ ርክብክብ ተደረገ።

አረካ: ነሐሴ 8 ቀን 2018 ዓ.ም

‎ኢንስቲትዩቱ በአረካ ግብርና ምርምር ማዕከል ለአነስተኛ መስኖ አገልግሎት የሚውል 250 ሜትር ጥልቀት ያለው ሁለተኛው የከርስ ምድር ውኃ ቁፋሮ ሥራ ለማከናወን ኤለጋንስ ኢንጂነሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ቀደም ስል በገባው ውል መሠረት የቦታ ርክብክብ አደርጓል።

በዕለቱ የተገኙት የኢንስቲትዩቱ ም/ዋና ዳይሬክተር ‎ዶ/ር ያሲን ጎአ ፕሮጀክቱ በ27 ሚሊዮን 6 ሺህ ብር ወጭ በ90 ቀናት ለማጠናቀቅ ውል የተገባ መሆኑና የሚገነባ መሆኑን ገልፀው አስፈላጊው ሁሉ ርብርብ በማድረግ ከውል ጊዜ ገደብ በፊት ማጠናቀቅ እንደሚገባ አሳስበዋል።

‎የፕሮጀክቱ ሥራ በምግብ ሥርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም (FSRP) ድጋፍ የሚከናወን ሲሆን፣ ‎ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ቀደም ሲል ተጀምሮ በመጠናቀቅ ላይ ካለው ሥራ ጋር 44 ሄክታር መሬት በመስኖ ማልማት የሚያስችል ወሳኝ መሠሠተ ልማት መሆኑን የማዕከሉ ዳይሬክተር ዶ/ር ገነነ ገዛኸኝ ገልፀው ለስከታማነቱን አስፈላጊውን እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል።

በቦታ እርክብክቡም የኢንስቲትዩቱ የFSRP ፕሮጀክት አስተባባሪን ጨምሮ የማኔጅመንት አባላት፣ የማዕከል ማኔጅመንት እና አማካሪ መሐንድሶች ተገኝተዋል።

center

Great job!! .
13/08/2026

Great job!!
.

ከ27 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የሚገነባ የከርሰ ምድር ውኃ ቁፋሮ ውል ተፈራረመ።+++++++++++++++ነሐሴ 7 ቀን 2018 ዓ.ም   ‎ #ዲላ+++++++++++++++‎ኢንስቲትዩቱ  በአረካ ...
13/08/2026

ከ27 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የሚገነባ የከርሰ ምድር ውኃ ቁፋሮ ውል ተፈራረመ።
+++++++++++++++
ነሐሴ 7 ቀን 2018 ዓ.ም
‎ #ዲላ
+++++++++++++++

‎ኢንስቲትዩቱ በአረካ ግብርና ምርምር ማዕከል ለአነስተኛ መስኖ አገልግሎት የሚውል 250 ሜትር ጥልቀት ያለው የከርስ ምድር ውኃ ቁፋሮ ሥራ ለማከናወን ከኤለጋንስ ኢንጂነሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የውል ስምምነት ተፈራርመዋል።

‎ፕሮጀክቱ የ27 ሚሊዮን 6 ሺህ ብር ወጭ የሚገነባ መሆኑን ተገልጿል።

‎የፕሮጀክቱ ሥራ በምግብ ሥርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም (FSRP) ድጋፍ የሚከናወን ሲሆን፣ በሦስት ወራት ውስጥ ተጠናቆ ወደ ሥራ እንዲገባ በትኩረት ይሰራል ተብለዋል።

‎ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ 44 ሄክታር መሬት በመስኖ ማልማት የሚያስችል ሲሆን፣ በማዕከሉ የሚከናወኑ የግብርና ምርምር እና የመስኖ ልማት ሥራዎችን በከፍተኛ ደረጃ ለማጠናከር እንደሚያግዝ ተጠቁሟል።

‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አብዮት መብራቴ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ በክልሉ ውስጥ የመስኖ አማራጭ ልማቶችን ለማስፋፋት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፣ ይህን ዓይነት ፕሮጀክት በሌሎች የክልሉ አካባቢዎችም ተደራሽ ለማድረግ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አስታውቀዋል።


🌱 A HEARTFELT MESSAGE OF GRATITUDE 🌱"To the dedicated staff and community of Areka Agricultural Research Center:I extend...
03/08/2026

🌱 A HEARTFELT MESSAGE OF GRATITUDE 🌱

"To the dedicated staff and community of Areka Agricultural Research Center:

I extend my deepest appreciation to every single employee who stepped up today to plant over 2,000 seedlings!

Your hard work and enthusiasm are a shining contribution to our national historic initiative of planting 800 Million Seedlings in a Single Day. Together, we are building a greener, more resilient future for generations to come."

Dr. Genene Geahegn
Center Director

ከ2,000 በላይ  #የአቦካዶና  #ቡና  ችግኞች ተተከሉ።​ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ምየአረካ የግብርና ምርምር ማዕከል በመላ አገሪቱ በተካሄደው እና በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን...
03/08/2026

ከ2,000 በላይ #የአቦካዶና #ቡና ችግኞች ተተከሉ።

​ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም

የአረካ የግብርና ምርምር ማዕከል በመላ አገሪቱ በተካሄደው እና በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል በተካሄደው አገር አቀፍ የችግኝ መትከል ዘመቻ ላይ በንቃት ተሳተፈ። ማዕከሉ በዋናው ምርምር ጣቢያ ከ2,000 በላይ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን የአቮካዶ እና የቡና ችግኞች በይፋ ተክሏል።

​ይህ የችግኝ ተከላ ዘመቻ የአካባቢን ስነ-ምህዳር ከመጠበቅ ባለፈ የአካባቢውን ህብረተሰብ የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል ያለመ ነው። ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ የአቮካዶ ዝርያዎችን ከአገር በቀል ዛፎች ጋር አጣጥሞ መትከል የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚረዳ ሲሆን፣ የቡና ችግኝ እርሻን ማስፋፋት ደግሞ የኢትዮጵያን የቡና ሀብት በመጠበቅ የካካባቢውን አባወራዎች ኢኮኖሚያዊ ተፎካካሪነት ያሳድጋል።

​የማዕከሉ ዳይሬክተር ዶ/ር ገነነ ገዛኸኝ በወቅቱ እንደገለጹት፣ ማዕከሉ ከሚያዚያ ወር ጀምሮ የተለያዩ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞችን ስተክል መቆየቱን አስታውሰው ፣በቀጣዮቹ ቀናትም ይህ ዘመቻ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በመጠቆም፣ "በሳምንቱ ውስጥ ተጨማሪ 10,000 የቡና፣ የፍራፍሬ እና የአገር በቀል ዛፎች ችግኞችን ለመትከል የታቀደ ሲሆን ዝግጅቱም ተጠናቋል" ብለዋል።

​ማዕከሉ የሚያከናውናቸው እነዚህ የተከላ እንቅስቃሴዎች ለአፈር ጤና፣ ለአየር ንብረት መላመድ እና ለኢትዮጵያ የተፈጥሮ ቅርስ መጠበቅ ቀጥተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ በመሆናቸው፣ አረንጓዴና ጽዱ የወደፊት ኢትዮጵያን እድገትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ሀገራዊ ጥረት የሚያፋጥኑ ናቸው።

በስተመጨረሻም ከአጠቃላይ ሠራተኞች ጋር ቡና ጠጡ ፕሮግራም እና የሌማት ትሩፋት የሆነውን ማር በመቅመስ ፕሮግራሙ ተጠናቋል።

01/08/2026


 #ማስታወቂያ​🌱 800,000,000 Plantlets | 1 Day | 1 Unified Ethiopia 🇪🇹 #800,000,000  ሰኞ ሐምሌ 27 2018 ሀገር አቀፍ እና ክልል አቀፍ የአንድ ጀን...
30/07/2026

#ማስታወቂያ
​🌱 800,000,000 Plantlets | 1 Day | 1 Unified Ethiopia 🇪🇹

#800,000,000

ሰኞ ሐምሌ 27 2018 ሀገር አቀፍ እና ክልል አቀፍ የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ቀን ሰለሆነ እኛም ከሁሉም ሠራተኞች ጋር የራሳችንን አሻራ የሚናሳርፍበት ቀን ይሆናል።

Address

SNNPRS,Wolaita, Ethiopia
Areka
79

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Areka Agricultural Research Center, SEARI posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share