19/04/2026
እንኳን ደስ አላችሁ!!
Congratulations!!
ኮርፖሬሽናችን በ2024/2025 በጀት ዓመት ባስመዘገበው የላቀ የሥራ አፈፃፀም ከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር የዕውቅና ሽልማት አበርክቶለታል።
የከተማና መሰረተ ልማት ሚንስትር 1000 ኮንትራክተሮችን ያሳተፈ የመሰረተ ልማት ፌስቲቫል ባካሄደው መድረክ በኮንስትራክሽን ኢንደስትሪው ዘርፍ የላቀ አፈፃፀም ያስመዘገቡ 20 ተቋራጮችን ለይቶ 10 ተቋራጮችን በደረጃ አንድ እና 10 ተቋራጮችን በደረጃ ሁለት ለይቶ የዕውቅና ሽልማት አበርክቷል።
በዚህ የዕውቅና መርሃ ግብር ላይ ኅብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን የላቀ አፈፃፀም ካስመዘገቡት ምርጥ አስር ተቋራጮች ውስጥ ሆኖ በመገኘቱ በዓይነቱ ከፍያለ ሃገር ዓቀፍ የዕውቅና ሽልማት ተበርክቶለታል።
ስለሆነም ለመላው የኅብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን አመራርና ሰራተኞች እንዲሁም ከኮርፖሬሽኑ ጋር አብራችሁ የምትሰሩ አጋርና ባለ ድርሻ አካላት ለዚህ ዕውቅና መገኘት የነበራችሁ ሚና ከፍተኛ በመሆኑ በድጋሜ እንኳን ደስ አላችሁ!!
በድካማችሁ፣ በጥረታችሁ እና በአብሮነታችሁ ለተገኘው የዕውቅና ሽልማት በእጅጉ ልትኮሩ ይገባል።
በመጨረሻም በየደረጃው የምትገኙ የተከበራችሁ የኮርፖሬሽኑ አመራርና ሰራተኞች ይህንን የዕውቅና ሽልማት እንደ አንድ ትልቅ መስፈንጠሪያ ተጠቅመን አሁን ያለውን ዓለማቀፋዊ እና ሃገራዊ የኮንስትራክሽን ፈተናዎችን የሚያሻገሩ መፍትሄዎችን መጠቀም ይጠይቃል።
ይህ ሲሆን በሁሉም ፕሮጀክቶቻችን ለመፈፀም የታቀደውን አሳክተን 2025/2026 በጀት ዓመት ከዳግም የዕውቅና ሽልማት ባሻገር በዕራያችን ያመላከትነውን በምስራቅ አፍሪካ የኮንስትራክሽን ኢንደስትሪ ገብያ ውስጥ ለመቀላቀል የሚያስችለውን ሁሉ ሆነን መዘጋጀት ይጠበቅብናል።
ኢንጅነር መብት አድማስ
CEO
ኅብር ኮንስትራክሽን
ነገን እንገነባለ!!!