Amhara Industry Parks Development Corporation

Amhara Industry Parks Development Corporation Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Amhara Industry Parks Development Corporation, Industrial Company, Bahir Dar.

መልካም በዓል
11/04/2026

መልካም በዓል

የአየር ንብረት ሚዛንን ለማስጠበቅ ኢንዱስትሪዎች ጉልህ አስተዋጽኦ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ተገለፀ፤የአማራ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የዋናው መ/ቤት አመራሮችና ሠራተኞችን ጨምሮ ለ...
09/04/2026

የአየር ንብረት ሚዛንን ለማስጠበቅ ኢንዱስትሪዎች ጉልህ አስተዋጽኦ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ተገለፀ፤

የአማራ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የዋናው መ/ቤት አመራሮችና ሠራተኞችን ጨምሮ ለሚመለከታቸው የቅርንጫፍ ጽ/ቤት እና የገጠር ሽግግር ማዕከላት ባለሙያዎች የአየር ንብረት ለውጥ ምንነትና የሚያስከትለውን ተጽዕኖ በተመለከተ በባህር ዳር ከተማ ከመጋቢት 29/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ2 ቀናት የቆየ ስልጠና ሰጠ፡፡

የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ብርሐኑ ጣምአለው የአየር ንብረት ለውጥ አለም አቀፍ አጀንዳ በመሆኑ የሁሉንም አካላት ተሳትፎ የሚጠይቅ ቁልፍ ጉዳይ መሆኑን በስልጠና መክፈቻ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ገልፀዋል። ኢትዮጵያም የአየር ንብረትን ሊያዛቡ የሚችሉ እንቅስቃሴዎችን የመከላከል ስራ እየሰራች መሆኑን የገለፁት አቶ ብርሃኑ በተለይም የኢንዱስትሪው ዘርፍ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የሚያሳድረው ተጽዕኖ ቀላል ባለመሆኑ የማኑፋክቸሪንግ እና የምግብ ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች በአካባቢ የአየር ንብረት ላይ ተፅዕኖ ከማድረሳቸው በፊት የአካባቢና ማህበራዊ ደህንነት ህጎችን መሰረት በማድረግ የቅድመ መከላከል ስራ ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

በስልጠና መድረኩ የአየር ንብረት ለውጥ ምንነትና መንስዔዎች፣ የሚያሳድሩት ተፅዕኖና የመከላከያ መንገዶችን በተመለከተ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የስራ ባልደረባ በሆኑት በአቶ እስማኤል መሀመድ እንዲሁም ተፈፅሯዊ የአየር ንብረት ሚዛንን ለማስጠበቅ ከኢንዱስትሪዎች ሊጠበቁ በሚችሉ ተግባራት ዙሪያ የአማራ ክልል የአካባቢ ጥበቃ ቢሮ የስራ ባልደረባ በሆኑት በአቶ መንገሻ አንዱዓለም ሠነዶች ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡

የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው በስልጠናው ያገኙትን ክህሎትና እውቀት መሰረት በማድረግ ኢንዱስትሪዎች የአየር ንብረት ሚዛንን እንዳያዛቡ ከባለሀብቶችና ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር ተቀናጅቶ በመስራት የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ ገልፀዋል፡፡

ለኢንዱስትሪ ልማት ተግተን እንሰራለን!!

የድንገተኛ አደጋ ውድመትን ለመቀነስ ቅድመ መከላከል ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለፀ፤የአማራ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ከባህር ዳር ከተማ አስተዳደር እሳትና ድንገተኛ አደጋ...
25/03/2026

የድንገተኛ አደጋ ውድመትን ለመቀነስ ቅድመ መከላከል ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለፀ፤

የአማራ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ከባህር ዳር ከተማ አስተዳደር እሳትና ድንገተኛ አደጋ መከላከል ጋር በመተባበር ለዋናው መ/ቤት፣ ለቡሬ የተቀናጀ አግሮ-ኢንዱስትሪ ፓርክ እና ለገጠር ሽግግር ማዕከላት የስራ መሪዎችና ባለሙያዎች በእሳትና ድንገተኛ አደጋ ምንነት ዙሪያ ስልጠና ሰጠ፡፡

የአማራ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በክልሉ የኢንዱስትሪ ልማት እንዲስፋፋ የበኩሉን ሚና እየተወጣ መሆኑንና ኮርፖሬሽኑ በሚያስተዳድራቸው ፓርኮችና ማዕከላት የእሳትና ሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች ከመከሰታቸው በፊት መደረግ የሚገባቸውን የቅድመ ጥንቃቄ ስራዎችና አደጋው ከተከሰተ የከፋ ጉዳት ከማድረሱ በፊት በምን አግባብ መቆጣጠር እንደሚገባ ግንዛቤ መፍጠር አስፈላጊ በመሆኑ ስልጠናው እንደተዘጋጀ የኮርፖሬሽኑ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጋሻው ወርቅነህ በስልጠና መክፈቻ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ገልፀው፤
ስልጠናውን በአግባቡ በመከታተል ባገኘነው ዕውቀት ላይ በመመሰረት በፓርኮች እና በማዕከላት የእሳትና ሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች እንዳይከሰቱ ከወዲሁ የቅድመ መከላከል ስራ ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡

በስልጠና መድረኩ ስለ ድንገተኛ አደጋ ምንነትና መከላከል ስራዎች፣ አደጋ ስለሚያስከትለው ማህበራዊ፣ ቁሳዊና አካላዊ ውድመት፤ የአደጋ ስጋት ምንጮችና የመከላከያ መንገዶች እንዲሁም የእሳት አደጋን ለመከላከል የህንፃዎች አሰራርና የመከላከያ መንገዶችን በተመለከተ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር እሳት አደጋ መከላከል ጽ/ቤት ባለሙያ በሆኑት በአቶ ተዋበ አንለይ እና በአቶ አንተነህ ፈቃዴ የስልጠና ሰነድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል፡፡

የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው ስልጠናው በግልም ሆነ በተቋም ደረጃ የእሳት አደጋ እንዳይከሰት ሊተገበሩ የሚገባቸው የቅድመ መከላከል ስራዎችን እና ከተከሰተም አደጋው ሊያስከትል የሚችለውን ውድመት ለመቀነስ ሊወሰዱ ስለሚገባቸው እርምጃዎች ግንዛቤ ማግኘታቸውን ገልፀው፤ በቀጣይ ባገኙት ግንዛቤ ላይ ተመስርተው ስራዎችን በልዩ ትኩረት እንደሚሰሩ ገልፀዋል፡፡

ለኢንዱስትሪ ልማት ተግተን እንሰራለን!!!

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ
21/03/2026

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ

እንኳን አደረሳችሁ!!
19/03/2026

እንኳን አደረሳችሁ!!

የስራ ቅጥር ማስታወቂያ
06/03/2026

የስራ ቅጥር ማስታወቂያ

የአማራ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የ2018 ዓ/ም የግማሽ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸሙን ገመገመ።የአማራ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የዕቅድ...
22/02/2026

የአማራ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የ2018 ዓ/ም የግማሽ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸሙን ገመገመ።

የአማራ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ የካቲት 14 2018 ዓ.ም በጎንደር ከተማ ተካሂዷል።

በውይይት መድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የጎንደር ከተማ ምክትል ከንቲባ ክብርት ወ/ሮ ደብሬ የኋላ ኮርፖሬሽኑ በክልሉ የኢንዱስትሪ ልማት እንዲስፋፋና ባለሀብቶች ወደ ኢንቨስትመንት እንዲገቡ እያደረገ ያለውን ጥረት አድንቀዋል። በቀጣይም ኮርፖሬሽኑ ተግባሩን ይበልጥ አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበው፤ የጎንደር ከተማ አስተዳደር የበኩሉን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልፀዋል።

የኮርፖሬሽኑ የዕቅድ ዝግጅት፣ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂና ሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ በልስቲ ወርቁ የኮርፖሬሽኑን የ2018 ዓ.ም የስድስት ወር የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትን ለመድረኩ አቅርበዋል። በሪፖርቱ ኮርፖሬሽኑ በስድስት ወሩ በቅድመ ዝግጅትና በተግባር ምዕራፍ የተከናወኑ ተግባራት በዝርዝር የቀረበ ሲሆን በመደበኛ እና በKPI ውጤታማ ተግባራትን ማከናወን እንደተቻለ ገልፀዋል።

የውይይት መድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ኮርፖሬሽኑ በቅድመ ዝግጅት ምዕራፍ ያከናወናቸው ተግባራት ለስድስት ወሩ ውጤታማነት መሠረት መሆናቸውን ገልፀው፤ የ2018 ዓመታዊ ዕቅድ በተሟላ መልኩ ለማሳካት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንደሚወጡ ጠቅሰዋል።

የአማራ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር አቶ ብርሃኑ ጣምአለው በበኩላቸው በስድስት ወሩ የታዩ ጥንካሬዎችን ይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባ፤ በተለያዩ ምክንያቶች ሳይከናወኑ የቀሩ ተግባራትን በልዩ ትኩረት መፈጸም እንዳለባቸው በውይይት መድረኩ ማጠቃለያ ላይ ገልፀው፤ለኮርፖሬሽኑ ዓመታዊ ዕቅድ ስኬት መላው የኮርፖሬሽኑ ሠራተኛና አመራር ርብርብ እንዲያደርግ አሳስበዋል።

በውይይት መድረኩ የኮርፖሬሽኑ አመራሮች፣ ዳይሬክተሮችና የቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

ለኢንዱስትሪ ልማት ተግተን እንሰራለን!!

በቀሪ 6 ወራት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድን ሙሉ በሙሉ ለማሳካት ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ፤የአማራ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የ2018 ዓ ም የ6 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ጥ...
24/01/2026

በቀሪ 6 ወራት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድን ሙሉ በሙሉ ለማሳካት ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ፤

የአማራ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የ2018 ዓ ም የ6 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ጥር 16/2018 ዓ ም በባህር ዳር ከተማ ገምግሟል።

በዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱ ባለፉት 6 ወራት በቅድመ ዝግጅትና በተግባር ምዕራፍ ከዋና ዋና ግቦች አኳያ የተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸም በዝርዝር ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

አፈጻጸሙ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የተሻለ አፈፃፀም የተመዘገበ መሆኑንና ከዕቅድ በታች የተከናወኑ ተግባራት አብዛኛዎቹ ተሻጋሪ ባህሪ ያላቸው ተግባራት በመሆናቸው አፈፃፀሙ በሚጠበቀው ልክ እንዳልሆነ የውይይቱ ተሳታፊዎች ገልፀዋል።

የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ብርሀኑ ጣምአለው በበኩላቸው በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ እንደገለፁት አፈፃፀሙ በጥቅል ተወስዶ ሲታይ አበረታች መሆኑን ጠቅሰው በዕቅዱ ልክ ያልተከናወኑ ተግባራትን በተለይ ከፕሮጀክት ግንባታ አኳያ በቀጣይ ወራት ልዩ ትኩረት ሰጦ መስራት እንደሚገባና የኮርፖሬሽኑን የ2018 ዓመታዊ ግቦች ለማሳካት በየደረጃው የሚገኝ የስራ መሪና ባለሙያ እጅና ጓንት ሆኖ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

ለኢንዱስትሪ ልማት ተግተን እንሰራለን!!

እንኳን አደረሳችሁ
18/01/2026

እንኳን አደረሳችሁ

06/01/2026

ኑ! በቡሬ የተቀናጀ አግሮ-ኢንዱስትሪ ፓርክ እና በገጠር ሽግግር ማዕከላት ኢንቨስት ያድርጉ

የቢዝነስ አማራጮችን ለመወሰን የኮርፖሬሽኑን የሀብት ግምት በአግባቡ ማወቅ እንደሚገባ ተገለፀየአማራ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የሀብትና ንብረት ግመታ ምንነትና አስፈላጊነትን በሚመለ...
06/01/2026

የቢዝነስ አማራጮችን ለመወሰን የኮርፖሬሽኑን የሀብት ግምት በአግባቡ ማወቅ እንደሚገባ ተገለፀ

የአማራ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የሀብትና ንብረት ግመታ ምንነትና አስፈላጊነትን በሚመለከት ለኮርፖሬሽኑ አመራሮችና ሠራተኞች ከታህሳስ 25-26/2018 ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ በአማራ ክልል ስቴት ዩኒቨርሲቲ ስልጠና ሰጠ፡፡

የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ብርሐኑ ጣምአለው በስልጠናው መክፈቻ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ኮርፖሬሽኑ ከክልሉ መንግስት የተሰጠውን የኢንዱስትሪ መሰረተ ልማት በማልማት ኢንቨስትመንትን የመሳብ፣የውጭ ምንዛሬ ግኝት የማሳደግ፣ተኪ ምርቶችን የማምረት፣ የስራ እድል ፈጠራ እንዲሁም የቴክኖሎጅ ሽግግርን ማሳለጥ አበይት ተልዕኮዎች በብቃት ለማሳካትና ትርፋማ ሆኖ በቀጣይ የቢዝነስ አማራጮችን ለመወሰን የኮርፖሬሽኑን የሀብትና ንብረት ግመታ በአግባቡ ማወቅ እንደሚገባ ገልፀው፤ ለዚህም ሳይንሳዊ እውቀት ማግኘት አስፈላጊ በመሆኑ ስልጠናው እንደተዘጋጀ ገልፀዋል፡፡

ስልጠናውን የሰጡት የባህር ዳር ዩንቨርስቲ መምህር አቶ አበበ ከቤ በበኩላቸው አንድ ድርጅት ትርፍና ኪሳራውን እንዲሁም የነገ ህልውናውን አውቆ ለመቀጠል ያለውን ሁሉንም የማይታይና የሚታይ ሀብት በትክክል ማወቅና የሀብት ግመታ መስራት አስገዳጅ እንደሆነ ገልፀው፣ ለዚህም በቂ እውቀትና ክህሎት ያለው አመራርና ባለሙያ መገንባት አስፈላጊ እንደሆነ ገልፀዋል። አቶ አበበ ከቤ አክለውም የአንድን ሀብት የዋጋ ግመታ የሚወስኑ ጉዳዮችንም በዝርዝር በስልጠናው አብራርተዋል፡፡

የስልጠና ተሳታፊዎች በበኩላቸው የስልጠና ርዕስ አመራረጥና አቀራረብ ከኮርፖሬሽኑ ተልዕኮ እና ድርጅታዊ ባህሪ አኳያ አመራሩና ሠራተኛው ሊኖረው የሚገባውን የእውቀትና ክህሎት ክፍተት የለየ በመሆኑ በቀጣይ የሀብትና ንብረት ግመታ በልዩ ትኩረት መሰራት እንዳለበት ገልፀዋል፡፡

በስልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ የኮርፖሬሽኑ ም/ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጋሻው ወርቅነህ ባስተላለፉት መልዕክት አንድ ድርጅት ተልዕኮውን ለማሳካት ጥረት ከማድረግ ጎን ለጎን ያለውን ሃብትና ንብረት በውል አውቆ መምራት ያለውን ጠቀሜታ በስልጠናው ግንዛቤ መገኘቱን ገልፀው፤ በቀጣይ ተግባሩን በተሟላ መልኩ ለመፈፀም ርብርብ እንደሚደረግ ጠቅሰዋል፡፡

ለኢንዱስትሪ ልማት ተግተን እንሰራለን!!!

Address

Bahir Dar
74

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Industry Parks Development Corporation posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Amhara Industry Parks Development Corporation:

Share