Central Ethiopia Region Electric Utility

Central Ethiopia Region Electric Utility የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት
Central Ethiopia Region Electric Utility

#ሆሳዕና

ለጎረቤት ሀገራት ከቀረበ የኤሌክትሪክ ሽያጭ ከ61 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ ተገኘሆሳዕና፣ የካቲት 25፣ 2017  ባለፉት 6 ወራት ለጎረቤት ሀገራት ከቀረበ የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ከ61 ሚ...
04/03/2025

ለጎረቤት ሀገራት ከቀረበ የኤሌክትሪክ ሽያጭ ከ61 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ ተገኘ

ሆሳዕና፣ የካቲት 25፣ 2017 ባለፉት 6 ወራት ለጎረቤት ሀገራት ከቀረበ የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ከ61 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡

የተቋሙ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ሞገስ መኮንን ለፋና ዲጂታል እንዳሉት ፥ የኃይል ማመንጨት ሥራ ላይ በትኩረት በመሥራት ለሀገር ውስጥና ለውጪ ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል የማቅረብ ሥራ እየተከናወነ ነው፡፡

በግማሽ በጀት ዓመትም 11 ሺህ 686 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ታቅዶ 13 ሺህ 504 ጊጋ ዋት ማመንጨት መቻሉን ተናግረዋል፡፡

ከተመረተው ኃይል ውስጥም ለጅቡቲ 274 ነጥብ 2 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ 17 ነጥብ 16 ሚሊየን ዶላር መገኘቱን ጠቅሰዋል፡፡

በተጨማሪም ለኬንያ 654 ነጥብ 9 ጊጋ ዋት ሰዓት እና ለሱዳን 26 ነጥብ 6 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ማቅረብ መቻሉን ነው ያስረዱት፡፡

ለሦስቱ ሀገራት ከቀረበ የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭም 61 ነጥብ 07 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡(Central Ethiopia Regional Government Communication Affairs bureau)

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጅነር ጌቱ ገረመው መልዕክት*****************የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኤሌክትሪክ ኃይል አቅራቢ ብቻ ሳይሆን የአገር ...
22/02/2025

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጅነር ጌቱ ገረመው መልዕክት
*****************
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኤሌክትሪክ ኃይል አቅራቢ ብቻ ሳይሆን የአገር ዕድገት መሠረት በመሆኑ በኢንዱስትሪ፣ በቱሪዝም፣ በግብርና፣ በማዕድን፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖጂ በአጠቃላይ በሁሉም የልማት ዘርፎች ያሉንን ጸጋዎች ለማልማትና ለመጠቀም የሚያስችል አቅም ነው፡፡

የኢትዮጵያን እድገት እውን ለማድረግ ብርሃን ፈንጣቂ ተቋምም ነው። እኔም በሚሊዮኖች የዕለት ተዕለት ኑሮ እና በአገራችን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ለውጦች ውስጥ ወሳኝ ሚና የሚጫወተውን ይህን ተቋም የመምራት እድል በማግኘቴ ታላቅ ክብር ይሰማኛል።

ከሁሉ አስቀድሜ የተቋሙ የእስካሁን ስኬቶች እና ያጋጠሙንን ፈተናዎች እውቅና መስጠት እፈልጋለሁ። የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦትን በማስፋፋትና አሰራሩን በማዘመን ረገድ በርካታ ስራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል፤በዚህም አበረታች ለውጦች መታየት ጀምረዋል፡፡

ሆኖም የደንበኞቻችንን እና የባለድርሻ አካላትን ፍላጎት ማርካት የሚያስችል አገልግሎት መስጠት ላይ ብዙ መስራት እንደሚጠበቅብን እገነዘባለሁ።

በተጨማሪም ከኃይል መቆራረጥ እንዲሁም ከአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት ጉድለት ጋር የተያያዙ በርካታ ችግሮች በመኖራቸው በውድ ደንበኞቻችን ዘንድ ቅሬታ መፍጠሩንም እረዳለሁ፡፡

እኔም የተሰጠኝን እድል በመጠቀም ከሌሎች የስራ ባልደረቦቼ ጋር በመሆን ከዚህ በፊት በተቋሙ የነበሩ መልካም አሰራሮችን በማስቀጠልና በማስፋት እንዲሁም ተቋሙ ያልተሻገራቸውን ተግዳሮቶች ስልታዊና ዘላቂ በሆነ መንገድ ለመፍታት ያላሰለሰ ጥረት እናደርጋለን፡፡

በእስካሁኑ አገልግሎታችን ያልረካችሁ እናንተ ውድ ደንበኞቻችንን እና ባለድርሻ አካላት ታላቅ ይቅርታ በራሴ እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ስም በትህትና እጠይቃለሁ፡፡

ከአገልግሎት አሰጣጡ ጋር በተያያዘ የደንበኞቻችንን እና የባለድርሻ አካላትን አስተያየት በማዳመጥና ቅሬታዎችን በፍጥነት በመፍታት ለማገልገል ዝግጁ መሆናችንን ለመግልጽ እፈልጋለሁ፡፡ በተቋማችን ላይ ያላችሁ እምነት ከፍ እንዲል በትጋትና በታማኝነት ለማገልግል እንሰራለን።

በዋነኝነት አስተማማኝና ጥራት ያለው የኤሌክትሪክ አገልግሎት መስጠት፣ ከብልሹ አሰራር የጸዳ አገልግሎት በፍትሀዊነት እንዲኖር ማስቻል፣ አገልግሎት አሰጣጡን ማዘመን፣ ፍትሀዊ የኤሌክትሪክ ተደረሽነትን እውን ማድረግ እንዲሁም ከውድ ከደንበኞቻችንና ባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ግንኙነት ማጠናከር የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎቻችን ናቸው፡፡

አስተማማኝና ጥራት ያለው የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለመስጠት እንዲቻል የኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማትን ማስፋፋትና የመልሶ ግንባታና የማሻሻያ ስራዎችን በስፋት ማከናወን እንዲሁም የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥን ለመቀነስ ከተቋረጠም ፈጣን የሆነ የአስቸኳይ ጥገና ስራ ማከናወን እና የተጀመሩ በቴክኖሎጂ የተደገፉ አሰራሮችን ተግባራዊ የማድረግ ስራን አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል፡፡

በአገልግሎት አሰጣጣችን ላይ ግልፅነትና ተጠያቂነትን በማረጋገጥ በውድ ደንበኞቻችን እና ባለ ድርሻ አካላት ዘንድ አመኔታ እንዲኖር ተሳትፎዋቸውን እያጠናከርን የተገልጋይ ስጋቶችን የሚመልስ ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት እንሰጣለን።

በተጨማሪም የትኛውም ተቋም ብቻውን ችግሮቹን ሊፈታ ስለማይችል ለቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት አሰጣጥ ከፌደራል፣ ከክልል መንግስታትና ተቋማት፣ አጋር የፋይናንስ ተቋማት፣ ከመገናኛ ብዙሃን እና ከግሉ ዘርፍ እንዲሁም ከማህበረሰቡ ጋር በቅርበት እንሰራለን፡፡ በተያያዘም ፍትሃዊ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ በትኩረት እንሰራልን፡፡

በመጨረሻም አገልግሎታችን ቀልጣፋ፣ ውጤታማ፣ ከብልሹ አሰራር የጸዳ ፍትሃዊነት የሰፈነበት ሆኖ በደንበኞቻችንና ባለድርሻ አካላት ዘንድ ተዓማኒነት እንዲኖረው የተቋማችን የስራ ባልደረቦች ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን የለውጥ ምዕራፍ በመገንዘብ ፈጠራ እና ፍጥነት በታከለበት ስሜት እንድታገለግሉ አሳስባለሁ፡፡

አመሰግናለሁ!!
ኢንጂነር ጌቱ ገረመው
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ

Ethiopian Electric Utility -የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

ጌቱ ገረመው (ኢ/ር) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ሆነው ተመደቡ ****************ጌቱ ገረመው (ኢ/ር) ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ ተቋሙን በዋና ስራ አስፈጻሚነት ...
21/02/2025

ጌቱ ገረመው (ኢ/ር) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ሆነው ተመደቡ
****************
ጌቱ ገረመው (ኢ/ር) ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ ተቋሙን በዋና ስራ አስፈጻሚነት ሲመሩ የቆዩትን ሽፈራው ተሊላ (ኢ/ር) በመተካት ተቋሙን በዋና ስራ አስፈጻሚነት እንዲመሩ ተመድበዋል፡፡

ጌቱ ገረመው (ኢ/ር) በተቋሙ የተለያዩ የስራ ሃላፊነቶች ላይ ለረጅም ዓመታት ሲያገለግሉ የቆዩ ናቸው፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

18/01/2025

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ !!

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብረሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ! በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የመተሳሰብ  እንዲሆንላችሁ እንመኛለን!! #የማዕከላዊኢትዮጵያክልልኤሌክትሪክአገልግሎት
06/01/2025

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብረሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ! በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ እንመኛለን!!

#የማዕከላዊኢትዮጵያክልልኤሌክትሪክአገልግሎት

ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብዎን  በቀላሉ፣ የትም ሳይሄዱ ባሉበት ሆነው ከዚህ በፊት በሚከፍሉበት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ካሻዎ በቴሌ ብር፣ በሲቢኢ ብር፣ በሞባይል ባንኪንግ፣ በአዋሽ ብር ፕ...
25/12/2024

ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብዎን በቀላሉ፣ የትም ሳይሄዱ ባሉበት ሆነው ከዚህ በፊት በሚከፍሉበት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ካሻዎ በቴሌ ብር፣ በሲቢኢ ብር፣ በሞባይል ባንኪንግ፣ በአዋሽ ብር ፕሮ ወይም በኤም ፔሳ በኩል ይፈፅሙ፡፡

ዘመናዊ የክፍያ አማራጮችን ምርጫዎ ያድርጉ! ዘመናዊ የክፍያ አማራጭ በመምረጥ ኑሮዎን ያቅሉ!

Via #የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

የከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቆጣሪዎች ሙሉ በሙሉ በኤ.ኤም.አይ ስማርት ቆጣሪዎች ተቀየሩ**********************በመላው ሃገራችን ያሉ የከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ነባር ቆ...
11/12/2024

የከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቆጣሪዎች ሙሉ በሙሉ በኤ.ኤም.አይ ስማርት ቆጣሪዎች ተቀየሩ
**********************
በመላው ሃገራችን ያሉ የከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ነባር ቆጣሪዎች ሙሉ በሙሉ በኤ.ኤም.አይ ስማርት ዘመናዊ ቆጣሪዎች መቀየራቸውን የኤ.ኤም.አይ ፕሮጀክት ኃላፊ አቶ ዘሪሁን አበበ ገለጹ፡፡

ከ24 ኪሎ ዋት በላይ ተጠቃሚ የሆኑ 39,463 ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ኤሌክትሮ ሜካኒካል ቆጣሪዎች ሙሉ በሙሉ በኤ.ኤም.አይ (Advanced Metering Infrastructure – AMI) ስማርት ቆጣሪዎች መቀየራቸውን ተናግረዋል፡፡

የ50 ሺህ ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ደንበኞችን ቆጣሪዎች በኤ.ኤም.አይ ስማርት ቆጣሪዎች ለመቀየር የታቀደ ቢሆንም ያሉት ደንበኞች 39,463 ብቻ በመሆናቸው ለነዚህ ደንበኞች ሙሉ በሙሉ መቀየሩን ኃላፊው ጠቅሰዋል፡፡

ቀሪዎቹ 10,537 ኤ.ኤም.አይ ስማርት ቆጣሪዎች ደግሞ ለአዲስ ደንበኞች እንዲውሉ ተደርጓል ብለዋል፡፡

ኤ.ኤም. አይ. ስማርት ቆጣሪ የቆጣሪ ስርዓቱ ከሰው ንክኪ ነፃ በመሆኑ ትክክለኛ የክፍያ ትዕዛዝ እንዲዘጋጅ እያገዘ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡

ደንበኞችም የዚህ ስማርት ቆጣሪ ተጠቃሚ በመሆናቸው ካሉበት ቦታ ሆነው የኤሌክትሪክ ፍጆታቸውን መከታተል ችለዋል ብለዋል፡፡

ነባሮቹ ኤሌክትሮ ሜካኒካል ቆጣሪዎች ከፍተኛ እድሜ ያስቆጠሩ በመሆናቸው በትክክል የኤሌክትሪክ ኃይል ፍጆታን ለመለካት አያስችሉም ነበር ሲሉ አቶ ዘርይሁን ገልጸዋል፡፡

በአሁኑ ሰዓት በኤ.ኤም.አይ ስማርት ቆጣሪ አማካኝነት ደንበኞች ትክክለኛ የፍጆታ ክፍያ እንዲከፍሉ ተቋሙም ትክክለኛ የኃይል ፍጆታ ሂሳብ እንዲሰበስብ ማድረግ ተችሏል፡፡

ከኤ.ኤም.አይ ስማርት ቆጣሪዎች የኃይል መቆራረጥን ድግግሞሽና ኤሌክትሪክ ተቋርጦ የሚቆይበትን መረጃ ማግኘት የተቻለ ሲሆን ይህም በቀጣይ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የማስተካከያ ስራ ለመስራት እንደሚያግዝ ይታመናል፡፡

የከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቆጣሪዎች ሙሉ በሙሉ በኤ.ኤም.አይ ስማርት ቆጣሪዎች ተቀየሩ
**********************
በመላው ሃገራችን ያሉ የከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ነባር ቆጣሪዎች ሙሉ በሙሉ በኤ.ኤም.አይ ስማርት ዘመናዊ ቆጣሪዎች መቀየራቸውን የኤ.ኤም.አይ ፕሮጀክት ኃላፊ አቶ ዘሪሁን አበበ ገለጹ፡፡

ከ24 ኪሎ ዋት በላይ ተጠቃሚ የሆኑ 39,463 ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ኤሌክትሮ ሜካኒካል ቆጣሪዎች ሙሉ በሙሉ በኤ.ኤም.አይ (Advanced Metering Infrastructure – AMI) ስማርት ቆጣሪዎች መቀየራቸውን ተናግረዋል፡፡

የ50 ሺህ ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ደንበኞችን ቆጣሪዎች በኤ.ኤም.አይ ስማርት ቆጣሪዎች ለመቀየር የታቀደ ቢሆንም ያሉት ደንበኞች 39,463 ብቻ በመሆናቸው ለነዚህ ደንበኞች ሙሉ በሙሉ መቀየሩን ኃላፊው ጠቅሰዋል፡፡

ቀሪዎቹ 10,537 ኤ.ኤም.አይ ስማርት ቆጣሪዎች ደግሞ ለአዲስ ደንበኞች እንዲውሉ ተደርጓል ብለዋል፡፡

ኤ.ኤም. አይ. ስማርት ቆጣሪ የቆጣሪ ስርዓቱ ከሰው ንክኪ ነፃ በመሆኑ ትክክለኛ የክፍያ ትዕዛዝ እንዲዘጋጅ እያገዘ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡

ደንበኞችም የዚህ ስማርት ቆጣሪ ተጠቃሚ በመሆናቸው ካሉበት ቦታ ሆነው የኤሌክትሪክ ፍጆታቸውን መከታተል ችለዋል ብለዋል፡፡

ነባሮቹ ኤሌክትሮ ሜካኒካል ቆጣሪዎች ከፍተኛ እድሜ ያስቆጠሩ በመሆናቸው በትክክል የኤሌክትሪክ ኃይል ፍጆታን ለመለካት አያስችሉም ነበር ሲሉ አቶ ዘርይሁን ገልጸዋል፡፡

በአሁኑ ሰዓት በኤ.ኤም.አይ ስማርት ቆጣሪ አማካኝነት ደንበኞች ትክክለኛ የፍጆታ ክፍያ እንዲከፍሉ ተቋሙም ትክክለኛ የኃይል ፍጆታ ሂሳብ እንዲሰበስብ ማድረግ ተችሏል፡፡

ከኤ.ኤም.አይ ስማርት ቆጣሪዎች የኃይል መቆራረጥን ድግግሞሽና ኤሌክትሪክ ተቋርጦ የሚቆይበትን መረጃ ማግኘት የተቻለ ሲሆን ይህም በቀጣይ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የማስተካከያ ስራ ለመስራት እንደሚያግዝ ይታመናል፡፡

Ethiopian Electric Utility -የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

ቡታጅራ ፣ ወራቤና በቡኢ አከበቢ ለሚኖሩ ደንበኞች በጥገና ምክንያት ህዳር 15/2017ዓም ኤሌክትሪክ የሚቋረጥ በመሆኑ ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ ለማሳሰብ።
23/11/2024

ቡታጅራ ፣ ወራቤና በቡኢ አከበቢ ለሚኖሩ ደንበኞች በጥገና ምክንያት ህዳር 15/2017ዓም ኤሌክትሪክ የሚቋረጥ በመሆኑ ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ ለማሳሰብ።

23/11/2024

ክቡራን ደንበኞቻችን የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮች ከዛፎች በሶስት ሜትር መራቅ እንዳለባቸው ያውቃሉ? እንግዲያውስ ይህንን ይገንዘቡ! ዛፎች ሲተከሉ ከኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት በሶስት ሜትር በማራቅ ይትከሉ !!

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

የሶስት ወር አፈጻጸም ተገመገመ*****የማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2017 ዓ.ም የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ግምገማ በሆሳዕና ከተማ ተካሄዷል።Photo by: Miskir
19/11/2024

የሶስት ወር አፈጻጸም ተገመገመ
*****
የማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2017 ዓ.ም የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ግምገማ በሆሳዕና ከተማ ተካሄዷል።

Photo by: Miskir

የምስራች ለክቡራን ደንበኞቻችን በሙሉ ************የተቋማችን የደንበኞች ኮንታክት ሴንተር ከ905 እና 904 ነፃ ጥሪ መስመሮች በተጨማሪ በዲጅታል አማራጭ አገልግሎት መሰጠት ጀመረ፡፡ ...
10/11/2024

የምስራች ለክቡራን ደንበኞቻችን በሙሉ
************
የተቋማችን የደንበኞች ኮንታክት ሴንተር ከ905 እና 904 ነፃ ጥሪ መስመሮች በተጨማሪ በዲጅታል አማራጭ አገልግሎት መሰጠት ጀመረ፡፡

ከክቡራን ደንበኞቻችን ከአገልግሎት አሰጣጣችን ጋር በተያያዘ የሚቀርቡ ቅሬታዎችና ጥቆማዎችን ለመቀበልና ለመፍታት ነፃ የጥሪ ማዕከል መዘረጋታችን ይታወቃል፡፡ በአሁን ወቅት ይህ የጥሪ ማዕከል ይበልጥ ለእናንተ ተደራሽ ለማድረግና አገልግሎቱንም ለማስፋት የዲጅታል አማራጭ በመጨመር ወደ ደንበኞች ኮንታክት ሴንትር አድጓል፡፡

በዚህም ማንኛውም ቅሬታዎችና ጥቆማዎችን በተቋማችን የፌስቡክ ገፅ 👉 https://web.facebook.com/EEUOfficial ቴሌግራም ገፅ 👉 https://t.me/eeuethiopia እንዲሁም አሁን ይበልጥ ተደራሽ ለመሆን በከፈትነው ቴሌግራም ግሩፕ 👉 https://t.me/EEUCustomersupport አማካኝት ቦታና ጊዜ ሳይገድባችሁ በቀላሉ ተደራሽ ማድረግ እንደምትችሉ ስንገልፅ በታላቅ ደስታ ነው፡፡

👉 የፌስቡክ ገፃችንን https://web.facebook.com/EEUOfficial
👉 እንዲሁም አዲሰ የከፈትነው የቴሌግራም ግሩብ (EEU Customers Digital Support) https://t.me/EEUCustomersupport

ሁላችሁም እንድትቀላቀሉና ሌሎችንም እንዲቀላቀሉ እንድታደርጉ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

09/11/2024

#የቅጥር ማስታወቂያ
***************
መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች በተጠቀሰው ቀንና ቦታ በመሄድ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን ::

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

አዲስ የኤሌክትሪክ ታሪፍ ማስተካከያ ተግባራዊ ሊደረግ ነው****************************የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ሽፈራው ተሊላ ዛሬ በሰጡት ...
04/09/2024

አዲስ የኤሌክትሪክ ታሪፍ ማስተካከያ ተግባራዊ ሊደረግ ነው
****************************
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ሽፈራው ተሊላ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አዲስ የኤሌክትሪክ ታሪፍ ማስተካከያ ተግባራዊ ሊደረግ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ተግባራዊ የሚደረገው የኤሌክትሪክ ታሪፍ ማስተካከያ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ሰኔ 13/2016 ዓ.ም መፅደቁን ያስታወሱት ዋና ስራ አስፈጻሚው፤ ከመስከረም 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ብለዋል፡፡

ዋና ስራ አስፈጻሚው በመግለጫቸው የታሪፍ ማሻሻያው በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ደንበኞችን እንዳይጎዳ ድጎማ መደረጉንና በህብረተሰቡ ሊያሳድረው የሚችለውን ጫና ለመቀነስ ድጎማ ከማድረጉም በተጨማሪ በየሩብ አመቱ ተከፋፍሎ ለአራት አመታት የሚተገበር መሆኑን ገልፀዋል፡፡

የሃገራችን የኤሌክትሪክ ታሪፍ ከሰሃራ በታች ካሉ የአፍሪካ ሃገራት የኤሌክትሪክ ታሪፍ ጋር ሲነጻጸር በጣም ዝቅተኛ መሆኑን የገለፁት ዋና ስራ አስፈጻሚው፤ አሁን ተግባራዊ የሚደረገው ማሻሻያ ከሁለት ዓመት በፊት መሻሻል የነበረበት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

እንደ ዋና ስራ አስፈጻሚው ገለፃ ተግባራዊ የሚደረገው ታሪፍ ማሻሻያ የተቋሙን የመልሶ ግንባታና ሌሎች ወጪዎችን ለመሸፈንና ጥራት ያለውና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለመስጠት ያለመ ነው፡፡

የታሪፍ ማሻሻያው የመኖሪያ ቤት፣ የንግድ ተቋማት፣ ዝቅተኛ ኢንዱስትሪ፣ ከፍተኛ ኢንዱስትሪ እንዲሁም የመንገድ መብራት ተጠቃሚ ደንበኞች በሚል መከፋፈሉንም አስታውቀዋል።

የመኖሪያ ቤት ተጠቃሚዎችን በተመለከተ እንደ አጠቃቀማቸው አሁን ከሚከፍሉትና ማስተካከያ ከተደረገበት መካከል ያለውን ልዩነት ሲከፍሉ እንደ አጠቃቀማቸው ድጎማ ተደርጓል፡፡

በዚህም ከ0 እስከ 200 ኪዋት/ሰ የሚጠቀሙ ደንበኞች የድጎማው ተጠቃሚ የሚሆኑ ሲሆን፤ ድጎማውም የመጨረሻው የትግበራ ዓመት ድረስ ይተገበራል ብለዋል፡፡

👉 ከ50 ኪዋት/ሰ በታች ለሚጠቀሙ ደንበኞች ያለውን ልዩነት 75 በመቶ የሚሆነውን ይደጎማሉ፣

👉 ከ50 ኪዋት/ሰ እስከ 100 ኪዋት/ሰ ለሚጠቀሙ ደንበኞች ያለውን ልዩነት 40 በመቶ የሚሆነውን ይደጎማሉ፣

👉 ከ200 ኪዋት/ሰ እስከ 300 ኪዋት/ሰ ለሚጠቀሙ ደንበኞች ያለውን ልዩነት 4 በመቶ ይደጎማሉ፣

👉 ከ400 ኪዋት/ሰ እስከ 500 ኪዋት/ሰ የሚሆነውን ማሻሻያውን ያለምንም ድጎማ የሚከፍሉ ይሆናል ብላዋል፡፡

እንዲሁም ከ500 ኪዋት/ሰ በላይ የሚሆነውን ደግሞ ሌላውን ተጠቃሚ የሚደግፉበት የጎንዮሽ ድጎማ ሥርዓት ተግባራዊ እንደሚደረግ አንስተዋል።

እንደ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገለጻ ይህ የተደረገው የታሪፍ ማስተካከያ የሚከፈለው በአንድ ጊዜ ሳይሆን በ16 ዙር በሚደረግ የሂሳብ ማስተካከያ [ከመስከረም 1/2017 ጀምሮ] በአራት ዓመት ጊዜ ውስጥ ተፈፃሚ ይሆናል።

ኢንጂነር ሽፈራው ይሄንን ሲያስረዱ 50 ኪዋት/ሰ የሚጠቀሙ ደንበኞች አሁን የሚከፍሉት 27 ሳንቲም እንደሆነ ገልጸው፤ ከመስከረም ጀምሮ የሚከፍሉት 35 ሳንቲም ይሆናል ብለዋል።

ከአራት ዓመታት በኋላ ደግሞ [በ16 ዙሮች በሚደረግ ማስተካከያ] 1.56 ብር መክፈል ይጀምራሉ ሲሉ አስረድተዋል።

ይህ አዲሱ የኤሌክትሪክ የታሪፍ ማስተካከያ አፈጻፀም ትግበራ የሚመለከታቸው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ የኢትዮጵያ ሃይል እና የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡

አዲሱን የታሪፍ ማስተካከያ የሚገልፅ መረጃ ለማግኘት ተከታዩን ሊንክ ይጫኑ፡-

http://www.eeu.gov.et/contents/electricity-tariff?lang=

ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ*********************External vacancy
22/07/2024

ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ
*********************
External vacancy

የጨረታ ማስታወቂያ!
06/06/2024

የጨረታ ማስታወቂያ!

04/06/2024

የተቋሙ ስራ አመራር ቦርድ አዲሱን የአሰራር ስርዓት ማሻሻያ አፀደቀ
**************
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሲያስጠናው የቆየው የአሰራር ስርዓት ማሻሻያ ትናንት ግንቦት 26 ቀን 2016 ዓ.ም በተቋሙ ስራ አመራር ቦርድ ፀድቆ ወደ ትግበራ ሊገባ መሆኑን የለውጥና መልካም አስተዳደደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እሱባለው ጤናው ገልፀዋል፡፡

እንደ አቶ እሱባለው ገለጻ ተቋሙ ተግባራዊ እያደረጋቸው ከመጡ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ጎን ለጎን የፓወር ሴክተሩን የሪፎርም አቅጣጫ በተከተለ መልኩ ውስጣዊ አሰራሩን፣ አደረጃጀቱን እንዲሁም የሰው ኃይል ብቃትን ለማሳድግ የሚያስችል አዲስ የአሰራር ስርዓት ማሻሻያ ሲጠና ቆይቶ ለትግበራ ተቃርቧል፡፡

ዳይሬክተሩ አክለውም ወደ ትግበራ የሚገባው የአሰራር ስርዓት ማሻሻያ ያልተማከለ አደረጃጀትን የተከተለ እንደሆነና ተቋሙ የሚሰጠውን አገልግሎት ስታንዳርዱን የጠበቀና ወጥነት ያለው ለማድረግ፣ ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት እንዲሁም የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ ይበልጥ በማዘመንና ተጠያቂነትን በማስፈን የደንበኞችን የእርካታ ደረጃ ለማሳደግ ጠቀሜታው የጎላ ነው ብለዋል፡፡

የአሰራር ስርዓት ማሻሻያው የተሻለ አገልግሎት እየሰጡ ከሚገኙ የሃገራችን ተቋማት ተሞክሮ በመውሰድ ጭምር የተዘጋጀ መሆኑን የገለፁት ዳሬክተሩ በየደረጃው የሚገኙ የስራ ሃላፊዎችን የመወሰን ስልጣን የሚያሳደግ፣ የሃብት አጠቃቀም ውጤታማነትን የሚያሻሽልና የአገልግሎት ተደራሽነትን የሚያሳድግ ነው ብለዋል፡፡

የአሰራር ስርዓት ማሻሻያውን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችሉ የትግበራ መመሪያዎች ተዘጋጅተው በስራ አመራር ቦርዱ መፅደቃቸውን የገለፁት ዳይሬክተሩ ከዚሁ ጋር ተያይዞ ማስተካከያ የተደረገበት ተቋማዊ አደረጃጀት፣ ስታፍ ፕላን፣ የሰራተኛ ምደባ መመሪያና ሌሎችም ከፀደቁት መመሪያዎች መካከል ይገኙበታል ብለዋል፡፡

የአሰራር ስርዓት ማሻሻያው በቀጣይ አምስት ወራት ውስጥ ሙሉ በሙሉ በሁሉም የስራ ክፍሎች ወደ ትግበራ ይሸጋገራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

በደ/ኤ/አገልገሎት ሆሳዕና ዲስትሪክት  #የወራቤ ፣  #የፎንቆና  #የሐዋሪያት ደ/አ/መ/ማዕከላት የቢሮ ግንበታ ተጠናቆ በቀን 23/09/2016 ዓ.ም በይፋ ተመረቀ።
31/05/2024

በደ/ኤ/አገልገሎት ሆሳዕና ዲስትሪክት #የወራቤ ፣ #የፎንቆና #የሐዋሪያት ደ/አ/መ/ማዕከላት የቢሮ ግንበታ ተጠናቆ በቀን 23/09/2016 ዓ.ም በይፋ ተመረቀ።

እንኳን ደስ አላችሁ!⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽አንጋፋው ኢትዮ ኤሌክትሪክ እግር ኳስ ክለብ ወደ ኢትዮጵያ ፕርመር-ሊግ ተመልሷል!አንጋፋው ኢትዮ ኤሌክትሪክ እግር ኳስ ክለብ ከፕርመር-ሊጉ ወደ ከፍተኛ-...
26/04/2024

እንኳን ደስ አላችሁ!
⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽
አንጋፋው ኢትዮ ኤሌክትሪክ እግር ኳስ ክለብ ወደ ኢትዮጵያ ፕርመር-ሊግ ተመልሷል!

አንጋፋው ኢትዮ ኤሌክትሪክ እግር ኳስ ክለብ ከፕርመር-ሊጉ ወደ ከፍተኛ-ሊግ በወረደበት ዓመት ወደ ኢትዮጵያ ፕርመር-ሊግ ተመልሶ አድጓል!

Address

Hossana
Hosanna

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Central Ethiopia Region Electric Utility posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category