Benatsemay Woreda Innovation and Technologe office

Benatsemay Woreda Innovation and Technologe office Information technology service

 #የኢትዮ ኮደርስ እና የBPR ጥናት!!የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ወስደዉ ሰረተፈኬት ላቀረቡ ባለሙያዎች: ስልጠና ስርተፋኬቱ  አንዱ የBPR መመዘኛ መስፈርት መሆኑን ያዉቃሉ...? 👉 ሃሳባቺሁን...
21/03/2026

#የኢትዮ ኮደርስ እና የBPR ጥናት!!

የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ወስደዉ ሰረተፈኬት ላቀረቡ ባለሙያዎች: ስልጠና ስርተፋኬቱ አንዱ የBPR መመዘኛ መስፈርት መሆኑን ያዉቃሉ...?
👉 ሃሳባቺሁን አስቀምጡ!

12/02/2026

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሰዎች ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ወስደዋል

ወላይታ ሶዶ፤ የካቲት 5/2018 (ኢዜአ):-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሰዎች ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መውሰዳቸውን የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮ ኃላፊው ቦጋለ ቦሼ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ዜጎች በነጻነት ለመንቀሳቀስ የሚያስችላቸው ነው።

መታወቂያው የዜጎችን ትክክለኛ ማንነት ለመለየትና የወንጀል ድርጊቶችን በመከላከል ለማህበረሰቡ ሁለንተናዊ ዋስትና መረጋገጥ ጠቀሜታ እንዳለውም አንስተዋል።

በክልሉም ነዋሪዎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት እንዲሆኑ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

እስካሁን መታወቂያውን ለማግኘት ከተመዘገቡት 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሰዎች ውስጥ 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን የሚሆኑት ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መውሰዳቸውን ተናግረዋል፡፡

16/01/2026
በደቡብ ኦሞ ዞን በበና ፀማይ ወረዳ የአንድ ጀንበር  የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ንቅናቄ መድረክ በይፋ እየተካሄደ ነው ::ጥር 07/2018 ዓ.ም ቀይ አፈር የበና ፀማይ ወረዳ ም/ አስተዳዳሪ አ...
15/01/2026

በደቡብ ኦሞ ዞን በበና ፀማይ ወረዳ የአንድ ጀንበር የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ንቅናቄ መድረክ በይፋ እየተካሄደ ነው ::

ጥር 07/2018 ዓ.ም ቀይ አፈር

የበና ፀማይ ወረዳ ም/ አስተዳዳሪ አቶ ሪራ ጉሎ
በሶስት ዓመቱ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና መረሃ ግብር በወረዳ ከ2 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች ስልጠናውን ለመስጠት ታቅዶ ወደ ተግባር እንደተገባ አሳውቀዋል ::

እስከ ዛሬ ወደ 1 ሺህ የሚሆኑ ዜጎች ስልጠናውን መውሰድ መቻላቸውን የገለጹት አቶ ሪራ ጉሎ አፈጻጸሙ ከዕቅድ አንጻር ዝቅተኛ ነው ብለዋል ::

በመሆኑም ስልጠናው በተፈለገው ደረጃ ግቡን አለመምታቱንም አቶ ሪራ ተናግረዋል ::

ስልጠናውን ስሰጥ የነበረው የዩዳ ሲቲ ካምፓኒ በቅርቡ ውሉን ልያቋርጥ ስለሚችል በቀሪ 6 ወራት ውስጥ ለ1 መቶ ሺህ ሰው ስልጠናውን ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል ::

በመሆኑም በዛሬው ዕለት በአንድ ጀንበር በወረዳ በሁሉም መዋቅሮች ከ1525 በላይ የሚሆኑ ሰዎች ስልጠናውን የሚወስዱ መሆኑን ተገልጿል ::

የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዮሐንስ ጋርሾ በመረሃ ግብሩ ተገኝተው ስልጠናውን ያስጀመሩ ሲሆን ስልጠናውን በግለሰብ ደረጃ መውሰድ ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅ በመሆኑ መንግስት ለዜጎች ስልጠናው በነፃ እንዲሰጥ በዲፖሎማሲ ማመቻቸቱን ተናግረዋል ::

ስልጠናው ለወጣቱ አቅም የምፈጥር ከመሆኑ ባሻገር የስራ ዕድል ጭምር የሚፈጥር እንደሆነ አቶ ዮሐንስ በመግለጽ ሁሉም እድሉን መጠቀም እንደሚገባ አሳስበዋል ::

ሁሉም ሰው ለስልጠናው ትኩረት በመስጠት ተከታትሎ ማጠናቀቅ እንዳለበት እና አመራሩ አስፈላጊውን ድጋፍ ሊያደርግ እንደሚገባም አቶ ዮሐንስ ገልፀዋል ::

የፋይዳ ቁጥር በተመዘገብኩ በስንት ቀን ይደርሰኛል?ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተመዝግበው ሲስተሙ ማንነትን በልዩ ሁኔታ ለይቶ ሲጨርስ ከጥቂት ሰዓታት እስከ ተወሰኑ የስራ ቀናት ውስጥ የፋይዳ ቁ...
24/12/2025

የፋይዳ ቁጥር በተመዘገብኩ በስንት ቀን ይደርሰኛል?

ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተመዝግበው ሲስተሙ ማንነትን በልዩ ሁኔታ ለይቶ ሲጨርስ ከጥቂት ሰዓታት እስከ ተወሰኑ የስራ ቀናት ውስጥ የፋይዳ ቁጥር በተመዘገቡበት ስልክ ቁጥር እና በተጨማሪም በኢሜይል አድራሻ ይደርስዎታል።

በተጠቀሰው ጊዜ ካልደረሰ ምን ማድረግ አለብኝ?

✏️ ወደ *9779 # በመደወል በራስዎ ማስላክ
✏️ በፋይዳ ቴሌግራም ቦት https://t.me/FaydaHelpBot መጠቀም
✏️ እንዲሁም የፋይዳ ሞባይል መተግበሪያን ተጠቅመው ማስላክ ይችላሉ።

በምዝገባ ወቅት ስህተት ስላጋጠመዎት ፣ መረጃ ለውጥ ስላደረጉ ወይም የፋይዳ ቁጥር ስላልደረስዎት ደግመው መመዝገብ የለብዎትም። ነገር ግን ከብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም በተለያዩ ምክንያቶች "ደግመው ይመዝገቡ" የሚል መልዕክት ከደረስዎ ብቻ በድጋሚ መመዝገብ ይኖርብዎታል

12/12/2025
09/12/2025

ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030!

የኢትዮጵያ "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ብሔራዊ ስትራቴጂን በተመለከተ በሰፈረመቅድም፣ ፕሮጀክቱ ከዲጂታል ዘመን አደጋዎችና ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ልማትና ሉዓላዊነትን በማጎልበት የኢትዮጵያን የልማት ጎዳና በራሱ ለመቅረጽ ቁርጠኛ መሆኗን ቀጥላለች።

"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂ፣ በዓላማ፣ በቁርጠኝነትና በችሎታ ላይ የተመሠረተ ብሔራዊ ምላሽ መስጠት ነው::

ስትራቴጂው ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2030 ታላቅ ልማትን ለማስመዝገብ ያለውን ከፍተኛ ምኞት የሚያሳይ ሲሆን፣ በኢኮኖሚ፣ በመንግሥታዊ አስተዳደርና በማኅበራዊ ዘርፎች ላይ ከፍተኛ ለውጥ ለማምጣት ያለመ ነው።

ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘመን የምትመራባቸውን መርሆዎች ሲያብራሩ የዲጂታል ለውጡ በኢትዮጵያ ማንነትና እሴቶች የተደገፈ ሲሆን፣ ለሁሉም ዜጎች አካታች፣ ፍትሃዊ እና ትርጉም ያለው እንዲሆን ተደርጎ የተዘጋጀ ነው ።

ኢትዮጵያ እየተገነቡ ባሉ እንደ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ባሉ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች አማካኝነት፣ የዜጎችን ደኅንነት ማስጠበቅና ብሔራዊ ሉዓላዊነትን መጠበቅ ትቀጥላለች። በተጨማሪም፣ በዲጂታል ሥርዓት ውስጥ ማንም ወደ ኋላ እንደማይቀር ማረጋገጥ ወሳኝ ጉዳይ ነው።

ይህ ቁርጠኝነት በዋናነት በሰው ላይ ኢንቨስት ማድረግን ይጠይቃል። ይህም ከተሞችንና ገጠራማ አካባቢዎችን ከፍ የሚያደርግ፣ እንዲሁም ዲጂታል አስተሳሰብንና የፈጠራ ባህልን በማጎልበት ኢትዮጵያን ወደ አዲስ ዘመን የሁሉን አቀፍ ዕድገትና ብልጽግና እንዲመራት ለማድረግ መዘጋጀቱን ያመለክታል።

"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" በዓለም አቀፍ አጋሮችና በዜጎች ትብብር፣ የጋራ ዕድገት መንፈስን በማንፀባረቅ የሚተገበር ነው።

ኢትዮጵያ የራሷን የዲጂታል ልማት ጎዳና ስትቀይስ፣ "ጥንካሬ ያላት፣ ሉዓላዊ እና ለወደፊት ዕድሎች ዝግጁ የሆነች ዲጂታል ኢትዮጵያ" ለመገንባት መተባበርን ይጠበቅብናል::

በቴክኖሎጂ የሚመራውን ዓለም ለመረዳት የዲጂታል ክህሎትን ማዳበር ወሳኝ ነው። ኢትዮጵያ በሶስት አመታት ውስጥ 5 ሚልዮን ኮደሮችን በዌብ-ፕሮግራሚንግ፣ በአንድሮይድ ማበልፀግ፣ ዳታ ሳይንስ እና...
07/12/2025

በቴክኖሎጂ የሚመራውን ዓለም ለመረዳት የዲጂታል ክህሎትን ማዳበር ወሳኝ ነው።

ኢትዮጵያ በሶስት አመታት ውስጥ 5 ሚልዮን ኮደሮችን በዌብ-ፕሮግራሚንግ፣ በአንድሮይድ ማበልፀግ፣ ዳታ ሳይንስ እና አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፎች ለማፍራት ነጻ የኦንላይን ሥልጠና እድሎችን በማዘጋጀት እየሰራች ይገኛል።

የኮዲንግ መሠረታዊ ክህሎት ለማዳበር የሚያስችሉትን ነጻ የኦንላይን ስልጠና እድሎችን በዚህ ሊንክ የሚያገኙ ሲሆን [https://ethiocoders.et/](https://ethiocoders.et/) ይህ ቪዲዮ የምዝገባ ሂደቱን ያስረዳል ይከታተሉ፤ስልጠናውን በመውሰድ ክህሎትዎን ያዳብሩ፡፡

ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ የአዲሱ ትውልድ ቋንቋ ነው!!


የበና ፀማይ ወረዳ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት

🔗ለተጨማሪ መረጃዎች ከስር ባሉ ማህበራዊ ሚድያ አማራጮች ይከታተሉን!

https://t.me/s_i_tofficekeyafer

17/11/2025
👉 ዛሬ በቀን 03/03/2018 በቃቆ ከተማ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በንቅናቄ እየተመዘገቡ ይገኛል ።ህዳር 03/2018 ዓ.ም =============             ‎
12/11/2025

👉 ዛሬ በቀን 03/03/2018 በቃቆ ከተማ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በንቅናቄ እየተመዘገቡ ይገኛል ።

ህዳር 03/2018 ዓ.ም
=============

ቀጣይ የመንግስት ቁልፍ አቅጣጫዎች ውስጥ፡ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን 💯 ማድረስበክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ተብለው ከተቀመጡ ቁልፍ ተግባራት አንዱ የሆነ...
11/11/2025

ቀጣይ የመንግስት ቁልፍ አቅጣጫዎች ውስጥ፡ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን 💯 ማድረስ

በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ተብለው ከተቀመጡ ቁልፍ ተግባራት አንዱ የሆነው የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ትግበራ አሁን ላይ 28 ሚሊዮን ዜጎችን በማካተት በከፍተኛ አገራዊ ንቅናቄ እየተሠራ ነው።

በዚህም መሰረት በያዝነው ዓመት በመላው ሀገሪቱ ተደራሽነትን በማስፋት እና የብሔራዊ መታውቂያ ስርዓቱን በማጎልበት 40 ሚሊዮን ዜጎችን ለመመዝገብ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል።

ምስል፡ ከኢቢሲ የተወሰደ

Address

Key Afer
Jinka

Telephone

+251946554820

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Benatsemay Woreda Innovation and Technologe office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Benatsemay Woreda Innovation and Technologe office:

Share