Sidama Construction Works Corporation

Sidama Construction Works Corporation The Corporation aspires to be one of the leading construction companies in the region and in the country as well.

SIdama Construction Works Corporation(SCWC)
*******************************************************************
Sidama Construction Works Corporation (SCWC) was established following the final decentralization process of the former Southern Nations, nationalities, and people’s regional states and the disintegration of the former South Water Works Construction Enterprise (SWWCE). The corporation wa

s established to meet the infrastructure demand of the region’s society in accordance with the power given in Article 57(6) of the Regional Constitution, to the Executive Council of Sidama National Regional State with Regulation No. 30/2022 on December 6, 2023. Since its establishment it has been entering into contract with the regional water mines and energy bureau to carry out irrigation and water supply projects and also Building construction of various sizes. The corporation shall have the following responsibilities:
• Construction of dams, irrigation, water works, hydropower,
sewerage network, water well drilling, rehabilitation, and pumping
tests
• Construction of roads, bridges, buildings, integrated drainage
development, flood protection, and river diversion for different
purposes.
• Manufacture, import, sell, distribute, and rent different materials
and tools necessary for the fulfillment of its objectives.
• Issue bonds, use deposits as security, sell them, and get involved
in the stock market.
• Engage in various investment and development activities by
obtaining authorization of the authority.
• Carry out electromechanical work.
• Provide engineering-related consulting services related to water
works, roads, and building construction.

03/05/2026

የሲዳማ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከተቋቋመ ሁለት አመታትን ያስቆጠረ የግንባታ ተቋም ሲሆን ባለፉት ሁለት አመታት የክልሉ መንግስት የክልሉን ህብረተሰብ የንፁህ መጠጥ ዉሃ ሽፋን ለማሳደግ የሚያደርገውን ጥረት በማገዝ በንፁህ የመጠጥ ዉሃ አቅርቦት ዘርፍ ሰፊ ስራ ሲሰራ ቆይቷል፡፡
ኮርፖሬሽኑ ባለፉት ሁለት ዓመታት ከ2.3 ቢሊየን ብር በላይ የዉለታ ዋጋ ያላቸውን 24 ከከፍተኛ እስከ አነስተኛ የመጠጥ ዉሃ ግንባታ ፕሮጀክቶችን በተቋራጭነት ዉል በመግባት ሲገነባ ቆይቷል፡፡ በዚህም የከተሞች፣ የጤና ተቋማት፣ የማረሚያ ተቋማት እንዲሁም ሌሎች ለህብረተሰቡ አገልግሎት የሚዉሉ የመጠጥ ዉሃ ግንባታ ፕሮጀክቶችን ገንብቷል፡፡ በተለይም ከፍተኛ የዉሃ እጥረት ባለባቸው የከተሞች የንፁህ መጠጥ ዉሃ አቅርቦት ላይ በተቋራጭነት በመሳተፍ እስከ 2ሚሊየን ሊትር መያዝ የሚችሉ ትላልቅ የኮንክሪት ዉሃ ማጠራቀሚያ ገንዳዎች ግንባታ እና ትላልቅ የመስመር ዝርጋታ ሥራዎችን በመስራት የህብረተሰቡን የመጠጥ ዉሃ ችግር ለመቅረፍ የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡
በንፁህ መጠጥ ዉሃ አቅርቦት የተሻለ ነገን ለመገንባት እየሠራ የሚገኘው ኮርፖሬሽናችን በያዝነው በ2018 በጀት ዓመት እየገነባቸው ከሚገኙ ፕሮጀክቶች ዉስጥ በፌደራልና በክልሉ መንግስት ድጋፍ እየተገነቡ የሚገኙት የሀዋሳ ከተማ የፋራ ሂጣታ፣ የአለታ ጩኮ ከተማ እና የአለታ ወንዶ ከተማ ከፍተኛ የመጠጥ ዉሃ ግንባታ ፕሮጀክቶች የሚጠቀሱ ናቸው፡፡
#ሲኮሥኮ
ሚያዝያ 25/2018 ዓ.ም.
ጥራት ላለው ግንባታ-ሲኮሥኮ

ዉብ በሆነ መልኩ ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘው የሀዋሳ መሶብ አንድ ማዕከል የአገልግሎት መስጫ ህንፃ ሪኖቬሽንና ግንባታ ፕሮጀክት የግንባታ ሂደት- በምስልሲኮሥኮሚያዝያ 22/2018 ዓ.ም...
30/04/2026

ዉብ በሆነ መልኩ ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘው የሀዋሳ መሶብ አንድ ማዕከል የአገልግሎት መስጫ ህንፃ ሪኖቬሽንና ግንባታ ፕሮጀክት የግንባታ ሂደት- በምስል
ሲኮሥኮ
ሚያዝያ 22/2018 ዓ.ም
በጥራት አንደራደርም!

የአለታ ጩኮ ሩፎ ዋኤኖ ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ሂደት - በምስል
29/04/2026

የአለታ ጩኮ ሩፎ ዋኤኖ ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ሂደት - በምስል

የሩፎ ዋኤኖ ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ፡፡*************************************** የሲዳማ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬ...
28/04/2026

የሩፎ ዋኤኖ ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ፡፡
***************************************
የሲዳማ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን በሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት አለታ ጩኮ ወረዳ እየገነባው የሚገኘው የሩፎ ዋኤኖ ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ህንጻ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡
ኮርፖሬሽናችን በግንባታ ተቋራጭነት ከፌደራል ትምህርት ሚኒስቴር ጋር ዉል በመግባት በነሀሴ ወር 2017 ዓ.ም. መጨረሻ ግንባታዉን የጀመረው ይኸው ፕሮጀክት የመንታ የጂ+2 ህንጻ ግንባታ፣ የመማሪያና የአስተዳደር ቢሮ ክፍሎችን፣ ክሊኒክ፣ ወርክሾፕ፣ ላቦራቶሪ እና መጋዘን ክፍሎችን ያካተተ 19 ብሎክ ህንጻ ግንባታ እንዲሁም የጥበቃ ቤት ግንባታ የያዘ ፕሮጀክት ነው፡፡
የፕሮጀክቱን ግንባታ በተመለከተ የፕሮጀክቱ ዋና ሃላፊ ኢ/ር ነብዩ ስዩም በሰጡት ማብራሪያ በፕሮጀክቱ ያሉ 19 ብሎኮች የግንብ ስራ ተጠናቆ የጣራ ስራ እየተሰራ የሚገኝ መሆኑንና የጂ+2 ህንጻ ግንባታም በግንባታ ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡ እንደ ፕሮጀክት ሃላፊው ገለጻ የፕሮጀክቱን ግንባታ ለማፋጠን በቀንና ምሽት ፈረቃ ሲሰራ መቆየቱንና ግንባታው በጥሩ ደረጃ ላይ የሚገኝ መሆኑን ሆኖም ከተወሰነ ጊዜ ወዲህ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተፈጠረው ወቅታዊ የነዳጅ እጥረት በፕሮጀክቱ ስራ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ መፍጠሩን አንስተዋል፡፡
ፕሮጀክቱን በዉል ጊዜ ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የገለፁት የፕሮጀክቱ ሃላፊ አሁን ላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም 48% ላይ የሚገኝ መሆኑንና ከላይ የተጠቀሰው ችግር ከተፈታ የባከኑ ጊዜያት አካክሶ ለመስራት ጥረት እንደሚገደረግ ገልፀዋል፡፡
#ሲኮሥኮ
ሚያዝያ 20/2018 ዓ.ም.
ጥራት ላለው ግንባታ-ሲኮሥኮ

ግንባታው እየተፋጠነ የሚገኘው የሀዋሳ ከተማ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ የህንጻ ሪኖቬሽንና ግንባታ ፕሮጀክት የግንባታ ሂደት በምስል #ሲኮስኮሚያዝያ 15/2018 ዓ.ም
23/04/2026

ግንባታው እየተፋጠነ የሚገኘው የሀዋሳ ከተማ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ የህንጻ ሪኖቬሽንና ግንባታ ፕሮጀክት የግንባታ ሂደት በምስል
#ሲኮስኮ
ሚያዝያ 15/2018 ዓ.ም

የሲዳማ ክልል የመንግስት ልማት ድርጅቶች የብልፅግና ፓርቲ ኅብረት አባላት ኮንፍራንስ ተካሂዷል። ******************በሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የልማት ድርጅቶች ተቆጣጣሪ ባለስ...
22/04/2026

የሲዳማ ክልል የመንግስት ልማት ድርጅቶች የብልፅግና ፓርቲ ኅብረት አባላት ኮንፍራንስ ተካሂዷል።
******************
በሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የልማት ድርጅቶች ተቆጣጣሪ ባለስልጣን፣ የሲዳማ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን እንዲሁም የሲዳማ ዲዛይንና ግንባታ ድርጅት የብልፅግና አባል ሠራተኞችን በጋራ ያቀፈው ኅብረት "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ቃል የአባላት ኮንፍራንስ በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት አካሂዷል።

በኮንፍራንሱ የሲዳማ ክልል ብልፅግና ፖርቲ ቅ/ፅ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሸናፊ ኤልያስ ጨምሮ የክልሉ የልማት ድርጅቶች ተቆጣጣሪ ባለስልጣን ዳይሬክተር አቶ ካንቹላ ካንቤ፣ የሲዳማ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ሥራ አስፈፃሚ አቶ ኤልያስ ቲሮ፣ የክልሉ የሲዳማ ዲዛይንና ግንባታ ድርጅት ሥራ አስኪያጅ ኢ/ር ይርጉ ታደሰን እንዲሁም የሶስቱም ተቋማት አመራሮች እና የህብረቱ አባላት ተገኝተዋል።

በዚህ የአባላት የጋራ መድረክ የፓርቲው ማኒፌስቶ እና ሪፖርት ለአባላት ቀርቦ የጋራ ውይይት የተደረገ ሲሆን የኀብረቱ አመራሮች ምርጫም ተካሂዷል። በመጨረሻም ውይይቱ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል።
ሚያዝያ 14/2018 ዓ.ም.
#ሲኮስኮ

21/04/2026
ኮርፖሬሽናችን ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር እዉቅናና ምስጋና ተበረከተለት****************************************************************የሀዋሳ ከተማ አስተዳ...
19/04/2026

ኮርፖሬሽናችን ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር እዉቅናና ምስጋና ተበረከተለት
****************************************************************
የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በ2ኛውና 3ኛው ዙር የኮሪደር ልማት ስራ የከተማዋን ጥሪ ተቀብለው ሙያቸውን፣ ገንዘባቸውንና ጊዜያቸውን ሳይሰስቱ ላበረከቱ ግለሰቦች፣ ተቋማትና ድርጅቶች ባዘጋጀው የዕዉቅናና የምስጋና መድረክ ላይ ኮርፖሬሽናችን በኮንትራክተርነት ላበረከተው አስተዋጽኦ ዕውቅናና ምስጋና ተሰጥቶታል።

በትላንትናው ዕለት በተዘጋጀው በዚህ የዕዉቅናና ምስጋና መድረክ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ፣ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ እንዲሁም የክልሉና የከተማ አስተዳደሩ የካቢኔ አባላት፣ ኮንትራክተሮች፣ አማካሪ ድርጅቶች፣ ግብአት አቅራቢዎችና ግለሰቦች የተገኙ ሲሆን ከተማ አስተዳደሩ ለኮርፖሬሽናችን ያበረከተውን ዕዉቅናና ምስጋና የኮርፖሬሽናችን ዋና ሥራ አስፋጻሚ አቶ ኤልያስ ቲሮ ተረክበዋል፡፡

የከተማዋ ከንቲባ የክልሉን አስተባባሪ ኮሚቴ በተለይም ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞንና የካቢኔ አባላትን፣ የሀዋሳ ከተማ አስተባባሪና ካቢኔ አባላትን፣ በግንባታው የተሳተፉ ኮንትራክተሮችና አማካሪ ድርጅቶችን ጨምሮ ግብዓት አቅራቢዎችንና የመንግስት ተቋማትን፣ እንዲሁም በገንዘብና በጉልበት ተሳትፎ ያደረጉ ግለሰቦችን ላደረጉት ተሳትፎ ምስጋናና እውቅና የሰጡ ሲሆን የሀዋሳ ከተማ ነዋሪምችም የዚህ ልማት አካል በመሆናቸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
ፎቶ፡- ሀዋሳ ከተማ አስተዳደር
#ሲኮስኮ
ሚያዝያ 11/2018 ዓ.ም.
ጥራት ላለው ግንባታ-ሲኮስኮ
Follow Us on:
Sidama Construction Works Corporation
www.t.me/scw_corporation
www.tiktok.com/

እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ! የሲዳማ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ መልካም የትንሳኤ በዓል እንዲሆንላችሁ ይመኛል! መልካም በዓ...
12/04/2026

እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ! የሲዳማ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ መልካም የትንሳኤ በዓል እንዲሆንላችሁ ይመኛል! መልካም በዓል!

የሲዳማ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ጋር ዉል በመግባት በሻፋሞ ወረዳ እየገነባዉ የሚገኘዉ የሻፋሞ ጤና ጣቢያ ግንባታ ፕሮጀክት የፋዉንዴሽን ስራ እየተጠናቀቀ ይገኛ...
11/04/2026

የሲዳማ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ጋር ዉል በመግባት በሻፋሞ ወረዳ እየገነባዉ የሚገኘዉ የሻፋሞ ጤና ጣቢያ ግንባታ ፕሮጀክት የፋዉንዴሽን ስራ እየተጠናቀቀ ይገኛል፡፡ በኮንስትራክሸን ባለስልጣን አማካሪነት ግንባታው የሚካሄደው ይህ የጤና ጣቢያ ግንባታ ፕሮጀክት የተለያዩ የህክምና መስጫ ክፍሎች፣ ፋርማሲ እና የስታፍ መኖሪያ ጨምሮ የ16 ብሎኮች ግንባታን ያጠቃለለ ነው፡፡ ኮርፖሬሽናችን በየካቲት ወር መጀመሪያ ላይ ግንባታውን በመጀመር ወደ ስራ የገባ ሲሆን አሁን ላይ በፕሮጀክቱ የአፈር እና የፋዉንዴሽን ግንባታ ስራ እየተሰራ ይገኛል፡፡
የፕሮጀክቱ ሃላፊ ኢ/ር ገብሬ ታረቀኝ ፕሮጀክቱን በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ ለመከወን እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀው አሁን ላይ ከወቅታዊ የነዳጅ ሁኔታ እና ዝናብ ጋር በተያያዘ ማቴርያል በተፈለገው ልክ ለማቅረብ እንቅፋት ቢሆንም ይህንንም ተግዳሮት በመፍታት የባከኑ ጊዜያትን አካክሶ ለመስራትና ፕሮጀክቱን በታቀደለት የጊዜ ሰሌዳ ዉስጥ ለማከናወን ኮርፖሬሽናችን አስፈላጊውን ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ አንስተዋል::ፕሮጀክቱ አሁን ላይ 10% የፕሮጀክት አፈፃፀም ላይ ይገኛል፡፡
ኮርፖሬሽናችን በክልሉ የጤና አገልግሎት አቅርቦት እንዲዳረስ በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች በጤና ተቋማት ግንባታ በመሳተፍ የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡
#ሲኮስኮ
ሚያዝያ 3/2018 ዓ.ም

Address

Behind Addisu Gebeya, Around Street George Church
Tamizhagam

Opening Hours

Monday 8:30am - 5:30pm
Tuesday 8:30am - 5:30pm
Wednesday 2:30am - 11:30pm
Thursday 2:30am - 11:30pm
Friday 8:30am - 5:30pm
Saturday 8:30am - 12:30pm

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sidama Construction Works Corporation posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share