09/25/2022
የአዲስ ቼምበር እጩ ፕሬዝደንት
መልዕክቱን ሼር በማድረግ አጋርነታችንን እናሳየው
አዲስ ቼምበርን በፕሬዝደንትነት ለመምራት እየተወዳደረ ለሚገኘው ወንድማችን ኤዳኦ አብዲ መልካም እድል እንዲገጥመው እንመኛለን::
ወንድማችን Edao Abdi Wosho ይህን መልዕክት አስተላልፏል::
"የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት 16ኛ ጉባኤውን ሀሙስ መስከረም 12,2015 ያካሄዳል:: ሀገራዊ ንግድንና ቀጠናዊ ትብብርን: ወቅቱ የሚጠየቀውን የንግድ ሳይንስና አመራር በመጠቀም የንግዱን ማህበረሰብ በሚመጥን ብቃት ለማገልገል በቂ የንግድና ቀጠናዊ ዕውቀት ይዘን ውድድር ላይ ነን::" ብሏል
ይህ ተቋም ንግዱ ማህበረሰብን የሚወክል ሲሆን በዚህ ዘርፍ ላይ አብዛኛው ህዝበ ሙስሊም ተሳታፊ ነው:: ሙስሊሙ ማህበረሰብ በንግድ ስራ ላይ መሳተፍ ብቻ ሳይሆን የሚወክለውን ተቋምም በብቃት ሊመሩ የሚችሉ ብቁ ሰዎች አሉት::
በንግዱ አለም ስኬታማ የሆኑ እንዳሉ ሁሉ በተቋም አመራርም ክህሎቱ እና ብቃቱ ያላቸው ሙስሊሞች ሞልተዋል:: ይህን በተግባር ለማረጋገጥ ወንድማችን ኢዳኦ አብዲ ሁሉንም የንግዱ ማህበረሰብን በእኩል ለማገልገል እና ተቋሙን ትልቅ ደረጃ ለማድረስ "የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤትን በፕሬዝዳንትነት ለመምራት እየተወዳደረ ይገኛል::
ወንድማችን ኢዳኦ አብዲ የኢዳኦ ኢንተርናሽናል ትሬዲንግ ባለቤት እና ስራ አስኪያጅ ሲሆን በማኑፋክቸሪግ እና በግብርና ዘርፍ ተሰማርቶ የሚገኝ ለበርካቶች የስራ እድል የፈጠረ ኢትዮጵያዊ ነው::
የአዲስ ቼምበር የጠቅላላ ጉባኤ አባላትም የወንድማችን ኢዳኦን ያዳበረውን የንግድ ሳይንስ እና አመራር ጥበብ ከግምት ውስጥ በማስገባት የንግዱ ማህበረሰብን የሚመጥን አመራር ይኖር ዘንድ ምርጫችሁ ታደርጉት ዘንድ መልዕክታችን ነው::
የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት 16ኛ ጉባኤውን ሀሙስ መስከረም 12,2015 የሚካሄድ ሲሆን በዚሁ ጠቅላላ ጉባኤ ምርጫው ተካሂዶ ወንድማችን ኤዳኦ አብዲም ምኞቱ ተሳክቶ ተቋሙን በብቃት ለመምራት ይበቃ ዘንድ አላህ ያግዘው ዘንድ ዱዓችን ነው::
መልካም እድል ለወንድማችን
መልዕክቱን ሼር በማድረግ አጋርነታችንን እናሳየው