05/24/2026
በአንከሻ ጓጉሳ ወረዳና በአገው ግምጃ ቤት ከተማ አስተዳደሮች በጋራ የተዘጋጀ የብልፅግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።
በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ስር በሚገኙት በእነዚህ ሁለት አስተዳደሮች አዘጋጅነት በአገው ግምጃ ቤት ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው ይህ ህዝባዊ ሰልፍ፤ "በላቀ ሕዝባዊ ተሳትፎ፣ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ ነው። ሰልፉ ብልፅግና ፓርቲ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ያስመዘገባቸውን ስኬቶችና ለመጪዎቹ አምስት ዓመታት የነደፈውን ልማታዊ ጉዞ የሚደግፍ ሲሆን፣ ጎን ለጎንም የብልፅግና ፓርቲ የ"ይምረጡኝ" ቅስቀሳ እየተካሄደበት ይገኛል።